1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የወይዘሪት ቡርቱካን ሚዴቅሳ መታሰር

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 21 2001

ትናንት የታሰሩትን የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ሊቀ መንበር ለማስለቀቅ የሚችለውን ሁሉ ጥረት እንደሚያደርግ ፓርቲው አስታወቀ ።

https://p.dw.com/p/GPYC
ምስል AP GraphicsBank/DW

የፓርቲው የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና ምክትል የህዝብ ግንኙነት አቶ እንዳልካቸው ሞላ ዛሬ ለዶይቼቬለ እንደተናገሩት ትናንት ወይዘሪት ቡርቱካን ሚዴቅሳ ሲያዙ አብረዋቸው የነበሩት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም እና ሾፌራቸውም እንግልትና ድብደባ ደርሶባቸዋል ። ወይዘሪት ቡርቱካን ለምን እንደታሰሩና ትናንት በፕሬፌሰር መስፍንና በሼፌሩ ላይ ደረሰ የተባለውን ዕንግልት ለማጣራት ከፖሊስ ኮሚሽንና ከፍትህ ሚኒስቴር ማብራሪያ ለማግኘት ሞክረን አልተሳካልንም ።