የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ወቅታዊ መግለጫ
ረቡዕ፣ ሚያዝያ 13 2013ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ድርጅት ቢሆንም ለዓለም ሰላምና መረጋጋት እንዲሁም ልማት ከተመድ ጋር በጋራ የሚሰራው የአፍሪቃ ሕብረት በሦስትዮሽ ድርድሩ ላይ መፍትሔ ይሰጣል የሚል ፅኑ እምነት እንዳላት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል። የሱዳን ወታደራዊ ኃይል በወረራ ድንበር ጥሶ የያዘውን የኢትዮጵያ መሬት ለቅቆ እንዲወጣ እና ጉዳዩ በሰላም እንዲፈታ አሁን ድረስ ያልተለወጠ አቋም መያዟም ተገልጿል። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በግብፅ ትደገፋለች ባለቻት ሱዳን ከሰሞኑ 61 ኢትዮጵያዊያንን ይዛ መልቀቋን ሚኒስቴሩ አረጋግጧል። በሱዳን ተይዘው ከተለቀቁት 59ኙ ገበሬዎች ፣ ሁለቱ ሚሊሺያዎች መሆናቸውን የተናገሩት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ነገር ግን ሱዳን ጉዳዩን አስመልክቶ 61 የኢትዮጵያ ወታደሮችን ይዤ ለቅቄያለሁ ማለቷ የተሳሳተ መረጃ ነው ብለዋል።
ሰሎሞን ሙጬ
ሸዋዬ ለገሠ
እሸቴ በቀለ