1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዓለም ባንክና ምዕተ ዓመቱ የልማት ዓላማ

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 3 1998

የተመድ የምዕተ ዓመቱ የልማት ዓላማ፡

https://p.dw.com/p/E0ds


የተመድ የምዕተ ዓመቱ የልማት ዓላማ፡ በተለይ ድህነትን በግማሽ የመቀነሱን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ የትኞቹ ድርጅቶች፡ የትኞቹ መንግሥታት፡ የትኞቹ ተቋማት ድርሻ ሊያበረክቱ ይችላሉ? በዚሁ ጥያቄ ላይ ለመወያየት የዓለም ባንክ ትናንት በዋሽንግተን የሁለት ቀን ስብሰባ ጠርቶዋል። የኤኮኖሚ ተወካዮች፡ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካዮች፡ ጠበብትና ፖለቲከኞች የምዕተ ዓመቱን የልማት ዓላማ በተሳካ ሁኔታ ወደፊት ለማራመድ ምን ሊደረግ ይችላል በሚለው ሀሳብ ላይ በሰፊው ተወያይተዋል።