1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዓለም የምግብ ድርጅትና የአልሸባብ ዛቻ

ረቡዕ፣ የካቲት 24 2002

የዓለም የምግብ ድርጅት በእንግሊዘኛው ምህፃር WFP ለሶማሊያ የሚሰጠውን ዕርዳታ እንዲያቆም አልሸባብ የተባለው የሶማሊያን መንግስት የሚወጋው ቡድን ቢያስጠነቅቅም የምግብ ተቋሙ በሶማሊያ ዕርዳታ መስጠቱን ለመቀጥል መወሰኑን አስታውቋል ።

https://p.dw.com/p/MIps
ምስል AP

ደቡባዊ እና ማዕከላዊ ሶማሊያን የሚቆጣጠረውና አልቃይዳ ከተባለ አሸባሪ ቡድን ጋር ቁርኝት አለው የሚባለው አልሸባብ ባለፈው ዓመት እንዳደረገው ሁሉ ከትናንት በስተያም የዓለም የምግብ ድርጅት ለሶማሊያ የምግብ ዕርዳታ እንዳያቀርብ ማገዱን አስታውቋል ። የሮሙ ወኪላችን ተክለ እዝጊ ገብረ እየሱስ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል ።

ተክለ እዝጊ ገብረ እየሱስ ፣ ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ