1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የየመኑ ፕሬዝዳትና አሜሪካ

ሐሙስ፣ ጥር 24 2004

የዩመኑ ፕሬዝዳት ዓሊ አብደላ ሳሌሕ «ለሕክምና» በሚል ሠበብ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ተጉዘዋል። የዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣናት ሳሌሕ ሐገራቸዉ የሚቆዩት ሕክምናቸዉን እስኪጨርሱ ነዉ።ታዛቢዎች እንደሚሉት ግን የዩናይትድ ስቴትስ ግብዣ ከፍተኛ ሕዝባዊ ተቃዉሞ ለገጠማቸዉ

https://p.dw.com/p/13pFq
FILE - In this April 8, 2011 file photo, Yemeni President Ali Abdullah Saleh reacts while looking at his supporters, not pictured, during a rally supporting him, in Sanaa,Yemen. A government official says Yemeni President Ali Abdullah Saleh has been moved to the Defense Ministry hospital for treatment after being wounded in a rocket attack Friday, June 3, 2011 on his palace. (AP Photo/Muhammed Muheisen, File)
ARCHIV Jemen Präsident Ali Abdullah Salehምስል AP

ለሰላሳ-ሰወስት ዘመኑ አምባገነን ገዢ ወዳጅዋ የክብር መዉጪያ ከማበጀት የሚቆጠር ነዉ። ሳሌሕ አምስት ልጆቻቸዉንና ባለቤታቸዉን አስከትለዉ በኦማን በኩል ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ለመጓዝ ባለፈዉ እሁድ ከሰነዓ ከመነሳታቸዉ በፊት ያገራቸዉን ሕዝብ «ሳላዉቅ-በስሕተት» ላሉት ጥፋት ይቅርታ ጠይቀዋል።የዋሽግተኑ ወኪላችን አበበ ፈለቀ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።

አበበ ፈለቀ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዮ ለገሰ