የዩኔስኮ የቻይና አደራ ፈንድ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 9 2006ማስታወቂያ
የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት UNESCO ከህዝባዊት ቻይና ሪፐብሊክ መንግሥት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በ 8 የአፍሪቃ ሃገራት የመምህራን ሥልጠና ፕሮጀክት እያካሄደ ነው ። ቻይና 8 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ያደረገችበት የዚሁ የዩኔስኮ የቻይና አደራ ፈንድ ፕሮጀክት ተጠቃሚ ከሆኑት ሃገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ናት ። ፕሮጀክቱ በዘመናዊ የኢንፎርሜሽን ኮምኒኬሽን ቴክኖሎጂዎች የመምህራን ማሰልጠኛዎችን ብቃት ከፍ የማድረግ እቅድ አለው ። ፕሮጀክቱ የሃገሪቱን የትምህርት ጥራትም በማሳደግም ረገድ የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የፓሪስዋ ወኪላችን የሃይማኖት ጥሩነህ ዘገባ ያስረዳል ።
ሃይማኖት ጥሩነህ
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ