የያሲር አረፋት አሟሟትና ምርመራዉ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 18 2005ማስታወቂያ
የቀድሞዉ የፍልስጤም ራስ ገዝ መስተዳድር ፕሬዝዳት የያሲር አረፋት አሟሟትን ለማጣራት የሚደረገዉ ምርመራ ዛሬም ከስምንት ዓመታት በሕዋላ አልተጠናቀቀም።አረፋት በጠና በታመሙበት ወቅት ይጠቀሙበት በነበረዉ የጥርስ ቡሩሽና ይጠመጥሙት በነበረዉ ካፍያ ላይ በተደረገዉ ምርመራ ፖልኒየም ሁለት መቶ የተሰኘዉ ገዳይ መርዛማ ንጥረ ነገር ተገኝቶበታል።የገዳዩ መርዝ መገኘት በፍልስጤማዉያን ዘንድ አረፋትን ያስገደለችዉ እስራኤልነች የሚል ጥርጣሬ አስከትሏል። ሐኪሞች እንደሚሉት ግን በአረፋት ንብረት ላይ መርዛማ ንጥረ ነገር መገኘቱ ለፍልስጤሙ አንጋፋ መሪ ሞት ምክንያት መሆኑን አያረጋግጥም።በዚሕም ምክንያት የሲዊስ፥ የፈረንሳይ፥ የሩሲያና የፍልስጤም ሐኪሞች ዛሬ የአረፋትን ቀብር ከፍተዉ ከአረፋት አካል ላይ ለተጨማሪ ምርመራ ይጠቅማል ያሉትን ናሙና ወስደዋል።ሥለ ጉዳዩ የይፋዉን ወኪላችንን ግርማዉ አሻግሬን ስቱዱዮ ከመግባቴ በፊት በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
ግርማዉ አሻጋሪ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ