የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ሁኔታ
ሰኞ፣ ሐምሌ 18 2008ማስታወቂያ
በደቡብ ሱዳን እንደገና ያገረሸው የርስ በርስ ጦርነት ተጨማሪ ዜጎችን ከሃገራቸው እያሰደደ ነው ።ባለፈው ሳምንት በአንድ ቀን ውስጥ ብቻ 8300 ስደተኞች ኡጋንዳ መግባታቸው ተዘግቧል ። ዓለም ዓቀፉ የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን UNHCR እንዳስታወቀው ከዚህ ዓመት ጥር ወዲህ ይህን ያህል ቁጥር ያለው ስደተኛ በአንድ ቀን ኡጋንዳ ሲገባ ያለፈው ሳምንቱ የመጀመሪያው ነው ። ከደቡብ ሱዳን በስተደቡብ ወደ ምትገኘው ኡጋንዳ ባለፈው ሳምንት ብቻ የተሰደዱት ደቡብ ሱዳናውያን ከ24 ሺህ ይበልጣሉ። አብዛኛዎቹም ሴቶች እና ህጻናት ናቸው ። በተመሳሳይ ሁኔታ ደቡብ ሱዳናውያን ወደ ኢትዮጵያም መሰደዳቸው አልቆመም ። በኢትዮጵያ የUNHCR መስሪያ ቤት እንዳስታወቀው ግን ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ቁጥር ከቀድሞው አሁን እየቀነሰ ነው ። የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዝርዝሩን አዘጋጅቷል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ