1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ የፀጥታ ሁኔታ

ቅዳሜ፣ ሐምሌ 7 2004

የዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ የፀጥታ ሁኔታ በየቀኑ እየከፋ በመሄድ ላይ ነው። ዴን ኻግ ኔዘርላንድስ በሚገኘው ዓለም አቀፍ የጦር ወንጀለኞቹ መዳኛ ፍርድ ቤት በሚፈለጉት በቦስኮ ንታንጋንዳ የሚመራው M23 የተባለው የኮንጎ ዓማፅያን ቡድን ሚሊሺያዎች ባለፈው ሣምንት በምሥራቃዊ ኮንጎ ከፊል ሰሜን ኪቩን ተቆጣጥረዋል።

https://p.dw.com/p/15Xbc
ARCHIV - Schwer bewaffnete Rebellen sichern ein Gebiet in Rutshuru, Nord-Kivu, im Kongo, unweit der Hauptstadt Goma, am 22 November 2008. In der Erde des Kongo lagern Gold und Kupfer, Bauxit und Koltan. Gerade Koltan ist wegen seiner Verwendung beim Bau von Mobiltelefonen immer stärker gefragt. Für hunderttausende Menschen vor allem im Osten des Landes aber ist dieser Rohstoffreichtum ein Fluch und kein Segen. Statt Wohlstand bringen die Mineralien Tod und Zerstörung, Versklavung und Verlust der Heimat. Gleich mehrere Rebellengruppen finanzieren ihre Waffen und ihren Kampf mit dem illegalen Abbau von Mineralien. Sie zwingen die Bewohner umliegender Dörfer zu der gefährlichen Schürfarbeit. Beim Verkauf der kostbaren Mineralien gehen die Dorfbewohner dann leer aus. EPA/LUCAS DOLEGA +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture-alliance/dpa

በኮንጎ ያለው ሞንዩክ በሚል መጠሪያ የሚታወቀው የተመ ሰላም አስከባሪ ሠራዊት ወታደሮች አሁን በዚሁ አካባቢ ኅልውናውን ቢያጠናክርም፡ አሥራ አንድ የምሥራቅ እና ማዕከላይ አፍሪቃ ሀገራት፡ ኮንጎ እና ርዋንዳ ጭምር፡ ይህ በቂ አለመሆኑን በማመልከት፡ ዓማፅያኑን የሚደመስስ ዓለም አቀፍ የጦር ኃይል እንዲቋቋም ጥሪ አቅርበዋል። አዲሱ ተዋጊ የጦር ኃይል ካካባቢው ሀገራት የሚውጣጡ ወታደሮችን የሚያጠቃልልና በተመድ የሚረዳ እንዲሆን ለአፍሪቃ ህብረት ስብሰባ በአዲስ አበባ የተገኙት የሀገራቱ ውጭና መከላከያ ሚንስትሮች በአዲስ አበባ ባለፈው ሐሙስ ተስማምተዋል።

የዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ ፕሬዚደንት በጦር ወንጀል የሚፈለጉት የቀድሞው ጀነራል ቦስኮ ንታንጋንዳ ተይዘው ወደ ዴን ኻግ ፍርድ ቤት እንዲላኩ ከጠየቁ በኋላ ነበር ያማፂው ቡድን M23 ባለፈው ሚያዝያ ወር ንታንጋንዳን ለመደገፍ በተነሳሱ ከኮንጎ ጦር በከዱ ቱትሲ ወታደሮች የተቋቋመው። ዓማፅያኑ ከዩጋንዳ ጋ በሚያዋስነው ድንበር አካባቢ ያለውን ቡናጋንን ላጭር ጊዜ በያዙበት ወቅት ብዙ ያካባቢው ነዋሪዎች ወደ ዩጋንዳ በመሸሻቸው፡ ርዳታ የማቅረቡ ተግባር አዳጋች መሆኑን በዚያ የሚገኘው ድንበር የማይገድበው የሀኪሞች ድርጅት የጀርመን ቅርንጫፍ ኃላፊ ፍራንክ ደርነር አስታውቀዋል። አቅርቦቱ ተግባር
« እኛ ርዳታ እያቀርብን ባለንበት የዩጋንዳ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ ከ 10.000 የሚበልጡ የሚገኙ ሲሆን፡ ማስተናገድ ከሚገባው በላይ ተጨናንቆ ይገኛል። »
በተለይ በሰሜን ኪቩ ርዕሰ ከተማ ጎማ የፀጥታው ሁኔታ ከፍተኛ ውጥረት የሚታይበት ሲሆን፡ አልፎ አልፎም የተኩስ ልውውጥ ይሰማል። ለደህንነታቸው የሰጉት ይህንኑ ያማፂ ቡድን የጎረቤት ርዋንዳ መንግሥት ይረዳል በሚል አንድ የተመድ ከጥቂት ጊዜ በፊት ዘገባ ካወጣ ወዲህ በከተማይቱ ነዋሪዎችና በዚያ በሚኖሩ የርዋንዳ ዜጎች መካከል ውጥረት ተካሮዋል። በምሥራቃዊ ኮንጎ የሚታየውን ከፍተኛ የርዋንዳ ተፅዕኖን በመቃወም ሰሞኑን አደባባይ የወጡት የጎማ ነዋሪዎች ርዋንዳውያኑን ከሀገር እንዲወጡ ጠይቀዋል።
« እኛ የኮንጎ ዜጎች እውነቱን ለመናገር አያስፈራንም። ዓማፅያኑ ከጎረቤታችን ርዋንዳ ድጋፍ ያገኛሉ። »
ርዋንዳ ለ M23 ዓማፅያን አንዳችም ርዳታ ትሰጣለች መባሉን የርዋንዳ ፕሬዚደንት ፖል ካጋሜ በማስተባበል፡ ይህንኑ በተመለከተ የተመድ ጠበብት ያወጡት ዘገባ አንድን ወገን ብቻ አናግሮ የተጠናቀረ ሀቁን ያላንፀባረቀ ዘገባ ነው በሚል አጣጥለውታል።

Rwanda president at int'l aid forum Rwanda President Paul Kagame speaks at the opening ceremony of the 4th High Level Forum on Aid Effectiveness at a convention center in South Korea's largest port city of Busan on Nov. 30, 2011. Some 3,500 representatives from 160 countries are attending the international forum on development assistance. (Yonhap)/2011-11-30 13:45:34/ Keine Weitergabe an Drittverwerter.
ፕሬዚደንት ፖል ካጋሜምስል picture-alliance/dpa
FILE- In this June 30, 2010 file photo, Congolese former warlord Bosco Ntaganda in his national army uniform attends the 50th anniversary celebration of Congo's independence in Goma in eastern Congo. In a marked turnaround, Congo's president Joseph Kabila called Wednesday, April 11, 2012 for the arrest of Ntaganda, a notorious ex-warlord and army general, who has been allowed to walk freely despite an international indictment, an official said. Ntaganda is accused of using child soldiers for fighting in Ituri, in northeastern Congo, from 2002 to 2003. (Foto:Alain Wandimoyi, File/AP/dapd) +++Abweichende Namen: Tanganda, Ntanganda, Ntangana, Ntagenda, Baganda, Taganda
ንታንጋንዳምስል dapd

ፊሊፕ ዛንድነር/አርያም ተክሌ

መሥፍን መኮንን