የድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችና የገጠሟቸው ሳንኮች፣
ማክሰኞ፣ ኅዳር 28 2003ማስታወቂያ
እርግጥ ነው ፣ ትምህርት ተቋም ከመገንባት በፊት ፣ ቅድመ ጥናት ማካሄድ፣ ለተቋማት ፤ ለተማሪዎች የሚያስፈልጉትን አሟልቶ ማቅረብ ግድ ይላል። ለምሳሌ ያህል በቅርቡ በአንድ ዘገባችን ላይ እንዳወሳነው፣ የአክሱም ዩኒቨርስቲ አንዳንድ የመጽሐፍት መደርደሪያዎቹ፣ ባዶ በመሆናቸው፣ ከዴንቨር፣ ኮላራዶ ፣ ዩናይትድ እስቴትስ በበጎ አድራጎት 9 ቶን መጽሐፍት ተሰብስቦ ተልኳል።
በምሥራቃዊው ኢትዮጵያ በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች፣ በከፍሎች መጨናነቅ፣ በቦታ ርቀት፣ በውሃ እጥረትና በትኋን ጭምር እንደሚቸገሩ የሰማው ዘጋቢአችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ስለ ስለመፍትኄው ጭምር ኀላፊዎችን ለማነጋገር ያደረገው ጥረት አልሠመረለትም። የተማሪዎቹን ችግር ግን እንደሚከተለው አቅርቦታል።
አበበ ፈለቀ
ተክሌ የኋላ
ነጋሽ መሐመድ