1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዶክተር መረራ ክስ

ዓርብ፣ የካቲት 24 2009

ችሎቱ ዶክተር መረራ ለክሱ በጠበቆቻቸው በኩል የሚያቀርቡትን የመቃወሚያ ሀሳብ ለመስማት እና ባቀረቡት የዋስትና መብት ጥያቄ ላይ ብይን ለመስጠት ለመጋቢት 29፣2009 ዓም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል ።

https://p.dw.com/p/2Ybrq
Dr. Merera Gudina Addis Abeba Äthiopien Oromo Pressekonferenz PK
ምስል DW/Y.Egziabhare

Beri.AA (Cout hearing on Merera's case) - MP3-Stereo

ዛሬ ያስቻለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19 ነኛ ወንጀል ችሎት ልደታ ምድብ በኦሮሞ ፌደራላስት ኮንግረስ ፓርቲ ሊቀመንበር ዶክተር መረራ ጉዲና ላይ አቃቤ ህግ ያቀረበውን ክስ አዳምጧል ። አቃቤ ህግ ዶክተር መረራን አብሮ ከከሰሳቸው ከዶክተር ብርሃኑ ነጋ የአርበኞች ግንቦት ሰባት ሊቀ መንበር፣ ከአቶ ጅዋር ሞሀመድ የፖለቲካ እና የመብት ተሟጋች ፣የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ኢሳት እና የኦሮሞ ሚድያ ኔትወርክ ጋር በጋራ እንዲሁም በግል አጥፍተዋል ያላቸውን አቅርቧል ። ችሎቱ  ዶክተር መረራ ለክሱ በጠበቆቻቸው በኩል የሚያቀርቡትን የመቃወሚያ ሀሳብ ለመስማት እና ባቀረቡት የዋስትና መብት ጥያቄ ላይ ብይን ለመስጠት ለመጋቢት 29፣2009 ዓምተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል ። ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝር ዘገባ አለው ።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ