1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመን ኢትዮጵያውያን ማህበር

ማክሰኞ፣ ጥር 7 2005

ማህበሩ በአሁኑ ጊዜ 125 አባላት ሲኖሩት ከመካከላቸው 30 ያህሉ ኢትዮጵያውያን ናቸው ። የማህበሩ ዋነኛ አላማ ኢትዮጵያን ለጀርመናውያን ማስተዋወቅ ነው ። ለዚሁ ተግባርም ኢትዮጵያን የተመለከቱ መረጃዎችን በአመት 3 ጊዜ በሚያወጣው መፅሄትና በአመት አንድ ጊዜ በሚጠራው ጉባኤ አማካይነት ያቀርባል ።

https://p.dw.com/p/17KWg
Das Gelände der Gesamthochschule Kassel (GhK) mit dem Technik-Neubau (l), aufgenommen am 23.10.2001. Bei ihrer Gründung am 25. Oktober 1971 war die Gesamthochschule Kassel (GhK) die erste ihrer Art in der Bundesrepublik. Mit der geplanten Umwandlung der nordrhein- westfälischen Gesamthochschulen in Universitäten wird sie bald wohl auch die letzte sein. Trotz des Erfolgs des «Kasseler Modells» überlegt die Hochschule daher, den Namen Gesamthochschule fallen zu lassen und sich nach 30 Jahren nur noch Universität zu nennen. Das gestufte Studiensystem der jüngsten Universität Hessens soll aber nicht angetastet werden.
ምስል dpa - Fotoreport

የጀርመን ኢትዮጵያውያን ማህበር ከተመሰረተ ባለፈው መስከረም 17 አመት ሆኖታል ። የተመሰረተውም ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያየ የሙያ መስክ ይሰሩ በነበሩ ጀርመናውያን ነው ። ጀርመናውያኑ ማህበሩን የመሰረቱትም ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለመቀጠልና ስለ ኢትዮጵያም መረጃ ለመስጠት በማሰብ ነው ። በጥቂት ጀርመናውያን የተቋቋመው ይህ ማህበር ብዙም ሳይቆይ ኢትዮጵያውያንን አባላትንም አሰባሰበ ። የማህበሩ የቦርድ ፀሃፊ አቶ መስፍን አማረ ለዲቼቬለ እንደተናገሩት ማህበሩ በአሁኑ ጊዜ 125 አባላት ሲኖሩት ከመካከላቸው 30 ያህሉ ኢትዮጵያውያን ናቸው ። የማህበሩ ዋነኛ አላማ ኢትዮጵያን ለጀርመናውያን ማስተዋወቅ ነው ። ለዚሁ ተግባርም ኢትዮጵያን የተመለከቱ መረጃዎችን በአመት 3 ጊዜ በሚያወጣው መፅሄትና በአመት አንድ ጊዜ በሚጠራው ጉባኤ አማካይነት ያቀርባል ። ለመሆኑ ማህበሩ ስለ ኢትዮጵያ የሚሰጣቸው መረጃዎች ምን ላይ ያተኮሩ ናቸው ? አቶ መስፍን
የጀርመን ኢትዮጵያውያን ማህበር አቅም በፈቀደ መጠን የተቋቋመበትን ዓላማ ተግባራዊ በማድረግ ላይ መሆኑን አቶ መስፍን ይናገራሉ ። አቶ መስፍን ማህበሩ በ17 አመታት ውስጥ ካከናወናቸው ተግባራት አብይ የሚሏቸውን ገልፀዋል ።
የጀርመን ኢትዮጵያውያን ማህበር የዘንድሮው ጉባኤው እንደሁልጊዜው በካስል ከተማ በሚያዚያ አጋማሽ ላይ ያካሂዳል ። ከጉባኤው ትኩረቶች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንዲሁም ጥቅምና ጉዳቱ ነው ። ጉባኤተኞችም የኢትዮጵያ ተሞክሮአቸውን እንዲሚያካፍሉ አቶ መስፍን ተናግረዋል ።

Die "Spitzhacke" des US-amerikanischen Künstlers Claes Oldenburg steht am Montag (29.03.2004) am Ufer der Fulda in Kassel. Das rund zwölf Meter hohe Kunstwerk wurde anläßlich der documenta 7 im Jahr 1982 am Ufer verankert. Die Stadt Kassel will am Abend Hessens Ministerpräsidenten Roland Koch (CDU) ihre Bewerbung für die Kulturhauptstadt 2010 überreichen. Bei der Wahl einer hessischen Stadt hatte sich das Land frühzeitig für Kassel entschieden. 16 deutsche Städte wollen sich nach dem derzeitigen Stand um den Titel bewerben. Die Europäische Union will 2006 entscheiden, welcher dieser Kandidaten zum Zuge kommt. Foto: Uwe Zucchi dpa/lhe
ምስል picture-alliance/dpa

ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ