1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመን ውህደት አባት ሄልሙት ኮል

ማክሰኞ፣ መስከረም 22 2005

ከብዙ ጥረት በኋላ ኮል ለዚያን ጊዜው የሶቭየት ህብረት መሪ ሚካኤል ጎርባቾቭ የጀርመንን ውህደትና የሶቭየት ወታደሮችም ከምስራቅ ጀርመን እንዲወጡ ለማሳመን በቁ ። የበርሊን ግንብ በፈረሰ አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እ.ጎ.አ ጥቅምት 3 1990 የጀርመን ውህደት በሬችትና በፌሽታ ተከበረ ።

https://p.dw.com/p/16J2f
Bundeskanzler Helmut Kohl sitzt allein auf der Regierungsbank im Bonner Bundestag. Der CDU-Vorsitzende ist am 1.10.1982 von der neuen Regierungskoalition aus CDU/CSU und der FDP im Bundestag zum sechsten Kanzler der Bundesrepublik Deutschland gewählt worden. In der geheimen Abstimmung über das konstruktive Mißtrauensvotum zum Sturz von Bundeskanzler Helmut Schmidt votierten 256 der 495 anwesenden Parlamentarier für den bisherigen Oppositionsführer. Der Abstimmung ging eine fünfstündige Debatte über den Regierungswechsel voran. pixel
ምስል picture-alliance/dpa
Helmut Kohl wird zum Bundeskanzler vereidigt. Der CDU-Vorsitzende Helmut Kohl ist am 1. Oktober 1982 von der neuen Regierungskoalition aus CDU/CSU und FDP zum sechsten Kanzler der Bundesrepublik Deutschland gewählt worden. In der geheimen Abstimmung im Bundestag über das konstruktive Mißtrauensvotum zum Sturz von Bundeskanzler Helmut Schmidt (SPD) erhielt Kohl sieben Stimmen mehr als die erforderliche absolute Mehrheit von 249 Abgeordneten. 256 von 495 Parlamentariern gaben dem 52jährigen bisherigen Oppositionsführer ihre Stimme. Am 17. September endete nach 13 Jahren die sozialliberale Koalition in Bonn durch den Rücktritt der vier FDP-Minister Hans-Dietrich Genscher, Gerhart Baum, Josef Ertl und Otto Graf Lambsdorff, was zum Sturz der SPD-Minderheitsregierung führte.
ምስል picture-alliance/dpa

የጀርመን ውህደት አባት ሄልሙት ኮል
የቀድሞው የጀርመን መራሄ መንግሥት ሄልሙት ለመጀመሪያ ጊዜ መራሄ መንግሥት ከሆኑ ትናንት 30 አመት ሆናቸው። በጀርመን ፊደራል ሪፐብሊክ ታሪክ ረዥም ጊዜ ሥልጣን ላይ የቆዩት ኮል ምዕራብና ምሥራቅ ጀርመንን ዳግም በማዋህድ ትልቅ ሚና የተጫወቱ መሪ ናቸው ። የዛሬው አውሮፓና ጀርመን ዝግጅታችን በኮልና ለጀርመን ውህደት ባደረጉት አስተዋጽኦ ላይ ያተኩራል ። ለቅንብሩ ሂሩት መለሰ ።

የጀርመን ፌደራል ሪፕብሊክ 6 ተኛው መራሄ መንግሥት ሄልሙት ኮል በጀርመን ታሪክ ልዩ ስፍራ የሚሰጣቸው መሪ ናቸው ። ለ 16 አመታት በተከታታይ ጀርመንን ከመምራታቸውም በላይ ለጀርመን ውህደት ብሎም ለአውሮፓ የፖለቲካ ና የምጣኔ ሃብት ህብረት የጎላ ድርሻ አበርክተዋል ። የበርሊን ግንብ ከመፍረሱ አንድ ቀን አስቀድሞ የያኔው የጀርመን መራሄ መንግሥት ሄልሙት ኮል ከርሳቸው በፊት መራሄ መንግሥት የነበሩት ሶሻል ዲሞክራቱ ቪሊ ብራንድት እንዲሁም ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃንስ ዲትሪሽ ጌንሸር በምዕራብ በርሊኑ የሾነንበርገር ማዘጋጃ ቤት ተገኝተው ንግግር አድርገው ነበር ። ብራንት ና ጌንሸር በያኔው ንግግራቸው ከምሥራቅ ወደ ምዕራብ ጀርመን ለመንቀሳቀስ የተገኘው የጉዞው ነፃነት ቀጥሎ ፣ የፖለቲካው ነፃነት መከተል እንደሚገባው ና የምሥራቅ ጀርመን ህዝብም የወደፊት እጣውን ራሱ መወሰን እንደሚገባው አሳሰቡ ። ኮል ግን በንግግራቸው ከዚህም የላቀ ጉዳይ ነበር ያነሱት

« በጀርመን ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ DDR ለተጨማሪ ነፃነትና ለእድገት የሚካሄደውን ለውጥ ለጀርመን ህዝብ አንድነት ስንል ባለብን የሞራል ግዴታ ድጋፍ እንሰጣለን ። ጉዳዩ የጀርመን ጉዳይ ነው ፤ የአንድነት ፣ የፍትህና የነፃነት ጉዳይ ነው ። ነፃው አባት አገር ጀርመን ለዘላለም ይኑር ፤ ነፃዋ አውሮፓችን ለዘላለም ይኑር »
ኮል በንግግራቸው የጠቀሱት ‚ነፃ አባት አገር ጀርመን ‘የሚለው አባባል የትልቋ ጀርመን መጥፎ ትዝታ ላላቸው ለተወሰኑ ግራ ኃይሎች ተንኳሽ አገላለፅ ነበር ። ጎረቤት የአውሮፓ አገሮችም ሳይቀሩ በበርሊኑ ግንብ መፍረስ ቢደሰቱም ይህን መሰሉ ስጋት አድሮባቸው ነበር ይሁንና በተወሰኑ ጀርመኖችም ሆነ በአውሮፓ ሃገሮች ላያ ያደረውን ይህን መሰሉን ስጋት ኮል ለማስወገድ ችለዋል ። ከብዙ ጥረት በኋላ ኮል ለዚያን ጊዜው የሶቭየት ህብረት መሪ ሚካኤል ጎርባቾቭ የጀርመንን ውህደትና የሶቭየት ወታደሮችም ከምስራቅ ጀርመን እንዲወጡ ለማሳመን በቁ ። የበርሊን ግንብ በፈረሰ አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እ.ጎ.አ ጥቅምት 3 1990 የጀርመን ለሁለት መከፈል ምልክት በነበረው በበርሊኑ የብራንድንቡርግ በር የጀርመን ውህደት በሬችትና በፌሽታ ተከበረ ።
ድምፅ……………………………………..ሪችት

BRD: Honecker-Besuch Nach der Begrüßung des Generalsekretärs des ZK der SED und Vorsitzenden des Staatsrates der DDR Erich Honecker, durch den Bundeskanzler Helmut Kohl vor dem Bundeskanzleramt in Bonn erklangen die Hymnen der beiden deutschen Staaten. Datierung: 7. September 1987 Fotograf: Oberst, Klaus Quelle: Bundesarchiv
ምስል Bundesarchiv - Bild 183-1987-0907-017


ኮል ራሳቸውን „አጋጣሚን መጠቀምን የታሪክን ካባ አጥብቆ ለመያዝ አስፈላጊ ነው „ በሚል ይገልጹት ነበር ። ልዩ ትኩረታቸው የነበረው ግን ራሷን ለቻለች የጋራ አውሮፓ ነበር ። የሉድቪክሃፈኑ ወጣቱ ሄልሙት ኮል ጦርነቱ ሲያበቃ ከቢጤዎቻቸው ጋር ወደ ፈረረንሳይ ድንበር ተጉዘው ነበር ። ፖለቲከኛ ከሆኑ በኋላም ኮል እንደዚህ ብለው ተናግረው ነበር ።
«ለኛ ለጀርመኖች የአውሮፓ አንድነት መርህን ይዞ መቀጠል የወደፊት እጣ ፈንታችንን እናኛነታችንን ወደ መጥፎ አቅጣጫ ያመራዋል ተብሎ የሚያከራክር ግልፅ ምክንያት አይኖርም ። የአውሮፓ አንድነት መርህ ከመከተል ውጭ ሌላ አሳማኝ አማራጭ አይኖረንም ። »
ከኮል ፍላጎቶች አንዱ ፣ ትክክለኛ ነው ብለው ያመኑበትን ሃሳብ ከፍፃሜ ለማድረስ ሥልጣን መያዝ ነበር ። ለዚህ ሊያበቃቸው ወደሚችለው የፖለቲካው አለም የገቡት በለጋ እድሚያቸው ነበር ። በ 17 አመታቸው ነበር የወግ አጥባቂው የጀርመን ክርስቲያን ዲሞክራት ህብረት ፓርቲ አባል የሆኑት ። ለመጀመሪያ ዲግሪያቸው በኋላም ለዶክትሬት ዲግሪያቸው ታሪክ ህግና የመንግሥት አስተዳደር ና መርህን በሚያጠኑበት ወቅት ኮል በፖለቲካው ንቁ ተሳታፊ ነበሩ ። በ 29 አመታቸው ራይንላንድፋልስ ፓርላማ ገቡ ። በ 33 አመታቸው ደግሞ በፓርላማው የ ፓርቲያቸው ሊቀ መንበር ሆኑ ።

Former German chancellor Helmut Kohl speaks 20 February 2002 at the French National Assembly during his hearing in front of the Foreign affairs commission. dpa
ምስል picture-alliance/dpa

በወቅቱ በጀርመን ፌደራዊ ክፍለ ሃገር ለዚህ ደረጃ በመብቃት ኮል በእድሜ ትንሹ ፖለቲከኛ ነበሩ ። ከ 6 አመታት በኋላም የፌደራል ክፍለ ሃገሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኑ ። 39 አመታቸው ነበር ያኔ ። ኮል በዚህ ሃላፊነት ለ8 አመታት አገልግለዋል ። እ.ጎ.አ በ1971 ለ ፓርቲያቸው ለክርስቲያን ዲሞክራት ህብረት ሊቀ መንበርነት አመልክተው ከ2 ዓመት በኋላ ተሳክቶላቸው እ.ጎ.አ ሰኔ 1973 የፓርቲውን ሊቀ መንበርነት ሥልጣን ያዙ ። በዚሁ ሥልጣናቸው 25 አመታት ቆይተዋል ።
ሊቀመንበር በሆኑበት እጎአ በ1970 ዎቹ መጀመሪያ አንስቶ ነበር ። «መራሄ መነግሥት መሆን እፈልጋለሁ ። ምርጫውን አሸንፌ መራሄ መንግሥት መሆን እፈልጋለሁ ። »
እጎአ በ1976 ይህ ምኞታቸው ወደ መሳካቱ ተቃርቦ ነበር ። እ.ጎ.አ በ1976 አጠቃላይ ምርጫ ኮል የእህትማማቾቹ የክርስቲያን ዲሞክራትና የክርስቲያን ሶሻል ህብረት እጩ ተወዳዳሪ ሆነው ቀረቡ ። በዚሁ ምርጫ 48.6 በመቶ ድምፅ አገኙ ። ይህም በፓርቲያቸው ታሪክ ሁለተኛ ደረጃ የሚይዝ ከፍተና ድምፅ ነበር ። ይሁንና በወቅቱ በሄልሙት ሽሚት ይመራ የነበረውን የሶሻል ዲሞክራቶቹንና የነፃ ዲሞክራቶቹን ጥምር መንግሥት ግን ማሸነፍ አልቻሉም ። ከ 6 አመት በኋላ እጎአ ጥቅምት 1 ፣ 1982 የዛሬ 30 አመት የኮል ምኞት ተሳካ ። ያኔ በፓርላማው በተሰጠ የመታመኛ ድምፅ ከሶሻል ዲሞክራቶቹ ፓርቲ ጋር ተጣምረው ይሰሩ የነበሩት ነፃ ዲሞክራቶች በመሪያቸው በሃንስ ዴትሪሽ ጌንሸር ቀስቃሽነት አፈንግጠው ከክርስቲያን ዲሞክራት ህብረት ጋር መጣመርን በመምረጣቸው የፌደራሉ መንግሥት ፈረሰና ኮል መራሄ መንግሥት ሆነው አዲስ አስተዳደር መሰረቱ ። ሥልጣን በያዙበት በጥቅምት 1 ፣ 1982 ባሰሙት የመርህ ንግግራቸው የመንፈስና የሞራል ለውጥ መካሄድ እንደሚገባና በትግሉ ውስጥ ግራዎቹ የያዙትንም አቋም በግልፅ አስረዱ ።

Die nordrhein-westfälische Ministerpräsidentin Hannelore Kraft (SPD) spricht am Montag (03.10.2011) beim Festakt zum "Tag der Deutschen Einheit" im WCCB, dem ehemaligen Bundestag, in Bonn. Das Fest zum 21. Jahrestag der Wiedervereinigung wird gemeinsam mit dem 65. Gründungstag Nordrhein-Westfalens bereits seit Samstag (01.10.2011) gefeiert. Foto: Rolf Vennenbernd dpa/lnw
ምስል picture-alliance/dpa


« የነፃ የንግድ ተቋማትና የግለሰቦችም ነፃ እንቅስቃሴ መንግሥት በበላይነት ከሚቆጣጠረውና ከሚጫነው አሰራር የተሻለ ነው የሚል እምነት አለን ። መፃኤ እድሉን በራሱ የሚወስን ዜጋ ላይ እምነት አለን »
እ.ጎ.አ በ 1983 በተካሄደ ወቅቱን ባልጠበቀ ምርጫ እጅግ አድካሚ ከሆነ የምርጫ ዘመቻ በኋላ ድል ተቀዳጁ ። ብዙም ሳይቆዩ በመንግሥታቸው አዲስ የምጣኔ ሃብትና የማህበራዊ መርህ ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ ። ከዚህ በኋላም በቀደሙት ዓመታት እጅግ ከፍተኛ የነበረው የጀርመን አመታዊ እዳ ማሽቆልቆለ ጀመረ ። ይሁንና የኮል መንግሥት ሥራ አጥነትን መቆጣጠር አልቻለም ። በዚህ የተነሳም የህዝብ ቅሬታ እየጨመረ በመምጣቱ የ1987 ቱ አጠቃላይ ምርጫ ውጤት ጥሩ የሚባል አልነበረም ። የጀርመን ውህደት አስቀድሞ ባይመጣ ኖሮ ኮል ቀጣዩን የ1990 ውን ምርጫ ማሸነፋቸው አጠራጣሪ ነበር ። እጎአ በ1980 ዎቹ መጨረሻ የሶቭየት ህብረቱ መሪ ሚካኤል ጎርባቾቭ ፕሬስቶሪካ ለውጥና ግላስኖስት ግልፅነት ብለው በጀመሩት የፖለቲካ መርህ ኮል ለዘለቄታው ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ።

Dancing On The Wall - Berliners sing and dance atop the wall to celebrate the opening of East-West German borders November 10. Thousands of East German citizens moved into the West after East German authorities opened all border crossing points to the West. In background is the Brandenburg gate. (AP Photo/Thomas Kienzle/str) 10. November 1989
ምስል AP

እጎአ ሰኔ 1989 ጎርባቾቭን በያኔው የምዕራብ ጀርመን ዋና ከተማ ቦን ተቀብለው ካስተናገዱ በኋላ የተለያዩ ድርጊቶች በፍጥነት ይከናወኑ ጀመር ። ከጥቂት ወራት በኋላ የበርሊኑ ግንብ ፈረሰ ። ሄልሙት ኮልም በፍጥነት ይለዋወጥ የነበረውን ሁኔታ በመጠቀም ሁለቱ የጀርመን ሪፐብሊኮች የሚዋሃዱበትን 10 ነጥብ የያዘ እቅድ አቀረቡ ። ያቀረቡት እቅድ ተቀባይነት አግኝቶም ምሥራቅና ምዕራብ ጀርመን የዛሬ 22 አመት ለመዋሃድ በቁ ። በወቅቱ ሁለቱ ጀርመኖች ከተዋሃዱ ኃይላቸው ይጠናከራል ብሄሔረተኛም ይሆናሉ የሚለውን ስጋት ለማለዘብም ሞክረዋል ። ኮል ለጀርመን ውህደት የተቻላቸውን ሁሉ ጥረት አድርገው ቢሳካላቸውም ውህደቱ ያስከተላቸውን መዘዞች ግን መቋቋም አልቻሉም ። ከውህደቱ በኋላ የመንግሥት ወጪዎች ከቁጥጥር ውጭ መሆን ጀመሩ ። በተዋሃደችው ጀርመን ያበበው የሥራ እድል ብዙም አልዘለቅም ። ሳይቆይ የሥራ አጡ ቁጥር እየጨመረ መጣ ። ያም ሆኖ ኮል እጎአ የ1994 ቱን ምርጫ ደካማ ተፎካካሪ ስላጋጠማቸው ማሸነፍ ቻሉ ። ሆኖም በቀጣዩ በ1998 ግን ከመሸነፍና ሽንፈታቸውንም በፀጋ ከመቀበል ውጭ ሌላ እድል አልነበራቸውም ።

ARCHIV - Drei junge Tuerkinnen, zwei davon mit Kopftuechern, sitzen am 2. April 2009 in Berlin am Potsdamer Platz auf einer Mauer. Migrationssprachen sollten genauso wie Englisch oder Franzoesisch in der Gesellschaft anerkannt und als Schulfaecher eingefuehrt werden. Deshalb appellierten am Montag, 26. April 2010, Politiker, Wissenschaftler und Interessenvertreter an die Verantwortlichen im Bildungswesen, die Herkunftssprachen als Teil des Fremdsprachenunterrichts anzubieten. (AP Photo/Gero Breloer) --- FILE - Young Turkish women from Berlin, two of them wearing scarfs, sit on a wall near Potsdamer Platz on Thursday, April 2, 2009 in Berlin. (AP Photo/Gero Breloer)
ምስል AP


« የተወዳደርነውና የተወዳደርኩት ምርጫውን ለማሸነፍ ነበር ። በምርጫው ግን ተሸንፈናል ። ሶሻል ዲሞክራቶቹና ና የቀይና አረንጌዴዎቹ ጥምረት ማሸነፋቸው ግልፅ ነው ። ስለ ውጤቱም የሚያከራክር አይደለም ። በዚህም ምክንያት ይህን አጋጣሚ በመጠቀም የኒደር ሳክዘስንን ጠቅላይ ሚኒስትር ጌርሃርድ ሽሩደርን ለአዲሱ እና በጣም አስፈላጊ ለሆነው ሥልጣን በመብቃታቸው ለሃገራችን ጥቅም በመረከባቸው መልካም ምኞቴን እገልፅላቸዋለሁ ። » ።
ኮል ከ 16 አመታት የመንግሥት መሪነት ከወረዱ በኋላ በጀርመን ፓርላማ የተቃዋሚዎችን ቦታ ያዙ ። በአመቱ በሥልጣን ዘመናቸው ከህግ ውጭ በሚስጥር የባንክ ሂሳብ ለፓርቲያቸው የገንዘብ እርዳታ ተቀብለዋል የሚል ዜና መሰራጨት ጀመረ ። ኮል መጀመሪያ ላይ ድርጊቱን አስተባብለው ኋላ ላይ ግን እውነትነቱን አምነዋል ። በቀጣዩ ምርጫ ያል ተወዳደሩት ኮል ከዚያን ጊዜ አንስቶ ከጀርመን የፖለቲካ መድረክ እንደተገለሉ ነው ። ኮል ለመጀመሪያ ጊዜ መራሄ መንግሥት የሆኑበት 30 ኛ አመት በጀርመን ታስቧል ። ይህ የተደረገውም ለጀርመንና ለአውሮፓ ውህደት ያደረጉት ጥረት ትልቅ አስተዋጾ ግምት ውስጥ በማስገባት ነው ።

ሂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ