1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመን የምረጡኝ ክርክር መድረክ

ሐሙስ፣ ነሐሴ 30 2005

ሶስት ሳምንት ግድም የቀረዉ የፌደራል ጀርመን ምርጫ የአገሪቱን ፖለቲከኞች፤ በየመድረኩ እያፎካከረ እና እያተቻቸ ፤የቃላት ጦርነቱ እየተጋጋለ፤ ህዝቡ የምርጫዉን ቀን በመጠባበቅ ላይ ነዉ።

https://p.dw.com/p/19clr
Gäste schauen am 01.09.2013 in der Ständigen Vertretung (StäV) in Berlin das einzigeTV-Duell vor der Bundestagswahl zwischen Bundeskanzlerin Merkel (CDU) und dem SPD-Spitzenkandidaten Steinbrück an. Foto: Kay Nietfeld/dpa
ምስል picture-alliance/dpa

በየአዉራ ጎዳናዉ ዳር ላይ፤ ህዝብ በሚበዛባቸዉ አካባቢዎች እና በየህንፃዉ ላይ የተለጠፉት የተለያዩ ፓርቲዎች አርማ እና መፈክር የምርጫዉ መዳረስን እያሳሰቡ የኛ የፖለቲካ መርኅ ይሻላል የሚለዉን ሃሳብ እያስተላለፉ ይገኛሉ። የአካባቢ ቀበሌዎችም የምርጫዉን ቀንና ህዝቡ ድምፅ የሚሰጥበትን ቦታ የሚጠቁም አድራሻን መምረጥ ለሚችለዉ ለየእያንዳንዱ ዜጋ ሁሉ በፖስታ አድራሻዎች አድርሰዋል። ይህን ሁሉ ተከትሎ የምርጫዉን ቀንና በተለይ ዉጤቱን ለመስማት በጉጉት የሚጠባበቀዉ ጥቂት አይደለም። ከጥቂት ዓመታት በፊት በጀርመን የተጀመረዉ የእጩ መራኄ መንግስታት የሚያካሂዱት የቀጥታ የቴሌቭዝን ስርጭት ክርክር በርካታ የጀርመን ነዋሪዎችን እንደ እግር ኳሱ ሁሉ በቴሌቭዝን መስኮት ዙርያ አሰባስቦ ስለ አገሪቱ ወቅታዊ ፖለቲካና የወደፊት ጉዞዉ አወያይቶአል። በጀርመን የሁለቱ እጩ መራሄ መንግስታት ያካሄዱትን የቀጥታ የቴሌቭዥን ክርክር በጀርመን የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን እንዴት ተመለከቱት? ይህ ዓይነቱ ልምድስ መቼ ጀመረ? የዕለቱ የዝግጅታችን የሚያተኩርበት ርእስ ነዉ፤ የድምጽ ማዳመጫዉን በመጫን ሙሉዉን ቅንብር ያድምጡ።

German Chancellor Angela Merkel and her challenger, the top candidate in the upcoming German general elections of the Social Democratic Party (SPD), Peer Steinbrueck, pose with TV hosts during their TV duel in Berlin, September 1, 2013. German voters will take to the polls in a general election on September 22. The hosts pictured are (from left): Stefan Raab (ProSieben), Anne Will (ARD), Maybrit Illner and Peter Kloeppel (RTL). REUTERS/ARD/Max Kohr/Pool (GERMANY - Tags: POLITICS ELECTIONS) FOR EDITORIAL USE ONLY. NOT FOR SALE FOR MARKETING OR ADVERTISING CAMPAIGNS. MANDATORY CREDIT. ATTENTION EDITORS: PICTURE TO BE USED ONLY IN RELATION TO THE TV DEBATE
ምስል Reuters

አዜብ ታደሰ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ