1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመን የምክር ቤት አባል በዚምባብዌ

ሰኞ፣ ሚያዝያ 22 2004

የጀርመን ምክር ቤት የደቡባዊ አፍሪቃ የልማት ማህበረሰብ የወዳጅነት ቡድን ኋላፊ እሽቴፈን ሊቢሽ እንደተናገሩት በዝምባዌ ትክክለኛ እና ነፃ ምርጫ እንዲካሄድ የደቡብ አፍሪቃው ፕሬዚደንት ጃኮብ ዙማ በፕሬዚደንት ሮበርት ሙጋቤ ላይ ጫና ማድረግ እንደሚገባቸው አሳሰቡ።

https://p.dw.com/p/14nIx
The heads of states of the Southern African Development Community (SADC) are seen at the Mulungushi International Conference Center in Lusaka, Zambia, Saturday, April 12, 2008. Southern African leaders are holding an emergency summit to find a resolution to Zimbabwe's deepening political crisis, but Zimbabwean President Robert Mugabe has refused to attend, underlining his growing isolation in the region and the world. (AP Photo/Themba Hadebe)***Zu Stäcker, Keine Krise in Simbabwe? - Schwache Signale vom SADC-Krisengipfel***
ምስል AP

የጀርመን ምክር ቤት የደቡባዊ አፍሪቃ የልማት ማህበረሰብ የወዳጅነት ቡድን ኋላፊ እሽቴፈን ሊቢሽ እንደተናገሩት በዝምባዌ ትክክለኛ እና ነፃ ምርጫ እንዲካሄድ የደቡብ አፍሪቃው ፕሬዚደንት ጃኮብ ዙማ በፕሬዚደንት ሮበርት ሙጋቤ ላይ ጫና ማድረግ እንደሚገባቸው አሳሰቡ።

የጀርመን ምክር ቤት የደቡባዊ አፍሪቃ የልማት ማህበረሰብ የወዳጅነት ቡድን ልዑካን መሪ እሽቴፈን ሊቢሽ የጀርመን ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ኮሜቴ አባልም ናቸው። ጀርመንን የደቡብ አፍሪቃ ችግር የተንሰራፋባቸው ሀገሮች ሁኔታ እንዳሳሰባት አስታውቀዋል። ሊቢሽ እንዳሉት በአህጉሪቷ በአጠቃላይ ዲሞክራሲ እንዲሰፍን የአፍሪቃ መሪዎች ትልቅ ሚና መጫወት እንደሚኖርባቸው፣ የአለም አቀፉ የፖለቲካ ስምምነት በምህፃሩ GPA በተግባር ላይ እንዲውል በተለይ የደቡብ አፍሪቃው ፕሬዚደንት ጃኮብ ዙማ ተጠያቂ ናቸው ብለዋል። ይህን ስምምነት የዝምባዌ ባለስልጣናት እኢአ 2009 ዓም በዝምባዌ ስልጣንን ለተለያዩ ወገኖች ያከፋፈለ መንግስት እንዲመሰረት ሲባል ፈርመዋል። እንደ ሊቢሽ የደቡብ አፍሪቃው ፕሬዚደንት ጃኮብ ዙማ ፤ የዝምባዌ ባልደረባቸው ሮበርት ሙጋቤን መቆጣጠር ይችላሉ። « አቶ ዙማ በሳዴክ ስር ዝምባዌን በተመለከተው የአለም አቀፉ የፖለቲካው ስምምነት ተግባራዊ የሚሆንበትን መንገድ የመፈለግ ኃላፊነት አለባቸው። እንደሚመስለኝ ባለፊት ወራት ሲፈፅሙት ከነበረው በላይ መስራት አለባቸው። በቅርቡ በአዲሱ ህገ መንግስት ላይ ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድና ትክክለኛ እና ነፃ ምርጫ የሚካሄድበት ቀን እንዲቆረጥ ጫና ማድረግ የሚኖርባቸው ይመስለኛል። ያንን ነው ዝምባዊያን ማግኘት ያለባቸው። ይህ መብት በብዙ የአለማችን ሀገሮች አለ። የዝምባዌ ህዝብ ለትክክለኛ እና ነፃ ምርጫ እራሱ መወሰን መቻል አለበት።»

Stefan Liebich, Mitglied des Deutschen Bundestages (Die Linke) Wer hat das Bild gemacht/Fotograf? Silvera Padori-Klenke Wann wurde das Bild gemacht? 28.04.2011 Wo wurde das Bild aufgenommen? Berlin, Bundestag Bildbeschreibung: Bei welcher Gelegenheit / in welcher Situation wurde das Bild aufgenommen? Bei Interview Wer oder was ist auf dem Bild zu sehen? Stefan Liebich, Mitglied des Deutschen Bundestages (Die Linke)
እስቴፈን ሊብሊሽምስል DW

የመጨረሻው የዝምባዌ ምርጫ የተካሄደው እኢአ በ2008 ነው። ምርጫው አመፅ እና ግፅት ያየለበት እንዲሁም የጠቅላይ ሚኒስትር ሞርገን እስቫንጋሪ ፓርቲ 200 አባላትን ህይወት ያስከፈለ ነበር። በመጨረሻም ፕሬዚዳንት ሙጋቤ ምርጫውን ማሸነፋቸውን አስታወቁ። ውጤቱን ያልተቀበለው ሳዴክ ጥምር መንግስት እንዲመሰረት ግፊቱን አጠናከረ። የሳዴክ አባል አገራት መሪዎች ቀጣዩ የዝምባዌ ምርጫ አዲሱ ህገ መንግስት ስራ ላይ ከዋለ በኋላ ምርጫ እንዲካሄድ መረለጋቸውን ሲያስታውቁ ይህን መልስ ነው ከፕሬዚዳንት ሙጋቤ ያገኙት።« በዚህ አመት ምርጫዎች ማካሄድ ይኖርብናል። ምርጫዎቹ ህገ መንግስት ኖረም አልኖረም መካሄድ ይኖርባቸዋል። ችግሩ ምን እንደሆነ ለ ሳዴክ እናሳውቃለን። ሳዴክ እርባነ ቢስ ሙከራ እንድናደርግ ሊነግረን አይችልም።»

Zimbabwean President Robert Mugabe attends the Southern African Development Community (SADC) Extraordinary Summit of Heads of State and Government at the Sandton Convention Centre in Johannesburg, South Africa, 09 November 2008. The ongoing political crisis in Zimbabwe as well as the conflict in the eastern Democratic Republic of Congo (DRC) are on the agenda for the talks scheduled for one day. EPA/JON HRUSA +++(c) dpa - Bildfunk+++
ሮበርት ሙጋቤምስል picture-alliance/ dpa

እሽቴፈን ሊቢሽ ለዝምባዌ አዲስ ህገ መንግስት የመንደፍ ሂደቱ የተሳካ እንዲሁን የደቡብ አፍሪቃው ፕሬዚደንት ጃኮብ ዙማ እንዲያረጋግጡ ይፈልጋሉ። የአካባቢው ባለስልጣናት ዙማ ጥንካሬ በሌለው የዝምባዌ መንግስት ተጣማሪዎችን እንዲሸመግሉ ጠይቀዋል። ዝምባዌን ከጎበኙ በኋላ የጀርመን የምክር ቤት ልኡክ ወደ ጎረቤት አገር ዛምቢያ ነው ያመሩት። በዛምቢያ ደግሞ ተቃራኒ ሁኔታ ነው ያስተዋሉት።

«በዛምቢያ ያለ አንዳች ግጭት የስልጣን ሽግግር ተካሂዷል። ይህ ለአፍሪቃ አህጉር ጥሩ ምሳሌ ይሆናል ብለን እናስባለን። እንዲሁ ለሳዴክ ክፍሎችም ለውጥ ያለ ግጭት ሊካሄድ እንደሚችል ያሳያል።»

እሽቴፈን ሊቢሽ በምሳሌነት ያነሱት ባለፈው አመት መስከረም ወር በዛምቢያ የተካሄደውን ምርጫ ነበር። በዚሁ ምርጫ ማይክል ሳታ ፕሬዚዳንት ሩጲያ ባንዳን በምርጫ አሸንፈው ስልጣን ይዘዋል። በርካታ የአለም አቀፍ ድርጅቶች ምርጫው የህዝቡን ፍላጎት ያንፀባረቀ እንደነበር ተናግረዋል።

ልደት አበበ

ሂሩት መለስ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ