1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመን የዉህደት ቀን

ረቡዕ፣ መስከረም 23 2005

22ኛዉ የጀርመን የዉህደት ቀን መታሰቢያ በዓል ዛሬ በመላ ሀገሪቱ ተከብሮ ዉሏል። የዘንድሮዉ በዓል በይፋዊ ደረጃ ፕሬዝደንት ዮአኺም ጋዉክና መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል በተገኙበት በሙኒክ ከተማ ነዉ ደምቆ የተከበረዉ። ምስራቅና ምዕራብ ጀርመን የተዋሃዱበት 22 ተኛ አመት ዛሬ በመላ ጀርመን ተከብሮ ዋለ ።

https://p.dw.com/p/16JQG
ምስል Getty Images


በስነ ስርዓቱ ላይ የጀርመን ፕሬዝዳንት ዮአሂም ጋውክና መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል እንዲሁም ከ1500 የሚበልጡ ባለሥልጣናትና ታዋቂ ሰዎች ተገኝተዋል። በአሉን ያስተናገደው የባየር ፌደራዊ ክፍለ ግዛት ጠቅላይ ሚኒስትር ኽርስት ዜሆፈር በስነ ስርዓቱ ላይ ባሰሙት ንግግር ውህደቱ እንዲሳካ ምክንያት የሆኑትን ሰዎች አመስግነዋል።
« የአንድነትና የነፃነቱን መንገድ የጠረገው በጀርመን ሶሻሊስት አንድነት ፓርቲ ላይ በግልፅ የተካሄደው አመፅ ነው ። ለነዚህ ሰዎች ትልቅ ምስጋና ማቅረብ ይገባናል ብዮ አስባለሁ ። እነዚህን ቁርጠኛ ሰዎች እግዚአብሄር ይባርክ !»
በሌላ በኩል ከዛሬ 15 አመት አንስቶ ሲደረግ እንደቆየው በዛሬው እለትም ጀርመን ውስጥ የሚገኙ ከ 600 መቶ በላይ መስጊዶች ለጎብኚዎች ክፍት ሆነው ውለዋል ። ዘንድሮ ትኩረቱ የእስልምና ስነጥበብና ባህል የሚል ነው ።

Feierlichkeiten zum Tag der Deutschen Einheit
ምስል dapd

በተለያዩ የጀርመን ከተሞችም በተለያዩ ዝግጅቶች በዓሉ የተከበረ ሲሆን በሙኒክ ከተማ ከ1,500 በላይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና እንግዶች መገኘታቸዉ ተገልጿል። የምዕራብና ምስራቅ ጀርመን ዉህደት ያመጣቸዉ ለዉጦች መኖራቸዉ እንዳለ ሆኖ በኤኮኖሚዉ ረገድ በህዝቡ ዘንድ አሁንም አለመርካት እንደሌለ ነዉ የሚነገረዉ። ይህንና ተያያዥ ጥያቄዎችን በማንሳት የበርሊኑ ወኪላችን ይላማ ኃይለሚካኤልን ስለበዓሉ አከባበር በስልክ ስቱዲዮ ከመግባቴ አስቀድሜ አነጋግሬዋለሁ፤

Feierlichkeiten zum Tag der Deutschen Einheit
ምስል dapd

ይላማ ኃይለሚካኤል

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ