1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርምን ምርጫ እና ኢትዮጵያዊ ስድተኛ በጀርመን

ሐሙስ፣ ነሐሴ 28 2001

ይሁንና የእሁዱ ምርጫ ዉጤት በሕዝብ አስተያየት፥ በመገናኛ ዘዴዎች ግምት፤ በፖሊተካ አዋቂዎች ትንታኔ ላይ የተመሠረዉን ግምት መገለባበጡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ትክክለኛ አቅማቸዉን በትክክለኛዉ መራጫቸዉ

https://p.dw.com/p/JOXR
ምስል DW

ጤና ይስጥልኝ እንደምን ዋላችሁ።የዛሬዉ ዝግጅታችን በጀርመን-ላይ ያተኮሩ ሁለት ጉዳዮችን ተጠናቅረዉበታል።የጀርመን ምርጫ እና የምርጫ ዝግጅት፥ የመጀመሪያዉ፥ ለስደተኞች መብትና ደሕንነት የሚቆረቆር-አንድ የጀርመን ተቋም ልሽልማት ከመረጠዉ ኢትዮጵያ ስደተኛ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ሁለተኛዉ ነዉ።ከመጀመሪያዉ እንጀምራለን።በሰወስት የጀርመን ክፍለ ሐገራት ባለፈዉ እሁድ የተደረገዉ ምርጫ ዉጤት እስከ ምርጫዉ ዕለት የነበረዉን እምነትና ግምት ገለባብጦታል።የእሁዱ ምርጫ ዉጤት ወትሮም እንደተጠበቀዉ በመጪዉ መስከረም አጋማሽ በሚደረገዉ ምርጫ ለሚፎካከሩት የፖለቲከ ፓርቲዎች ጥሩ የአቅም መለኪያ መሆኑ አልቀረም።

ይሁንና የእሁዱ ምርጫ ዉጤት በሕዝብ አስተያየት፥ በመገናኛ ዘዴዎች ግምት፤ በፖሊተካ አዋቂዎች ትንታኔ ላይ የተመሠረዉን ግምት መገለባበጡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ትክክለኛ አቅማቸዉን በትክክለኛዉ መራጫቸዉ ፍላጎት እንዲለኩ ከመረዳቱ ጋር የድንጋጤ፥-ፉከራ፣ የዉዝግብ-ቅርርብ የታቃራኒ በሮችንም ነዉ-የከፈተዉ።H

Yilma Hinz/Hirut Melesse/

Negash Mohammed