1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የገና በዓል አከባበር

ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 29 2007

የገና በዓል ልዩ ዝግጅት በተመለከተ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተለያዩ የአውሮጳ ሃገራት የሚገኙ ወኪሎቻችን የላኩት ዘገባ በተለይ በአውሮጳ የሚገኙ ስደተኞች በዓሉን እንዴት እንዳከበሩት ያስቃኛል። ዘገባዎቹ ከኢትዮጵያ፣ ከፈረንሣይ፣ ከጀርመን እና ከጣሊያን የተላኩ ናቸው።

https://p.dw.com/p/1EGLq
Äthiopisches Weihnachten QUALITÄT
ምስል DW/G. Tedla

የአዲስ አበባው ወኪላችን ዩሀንስ ገብረእግዚያብሄር በመዲና አዲስ አበባ ዞር ዞር እያለና ወደ ሌላ ከተማም ስልክ በመደወል በዓሉ እንዴት እየተከበረ እንደሆነ አጠያይቋል።

የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለሚካኤል በመዲና በርሊን እና አከባቢዋ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን አነጋግሮአል።

ፓሪስ ከተማ የሚገኙ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን የበዓል መንፈሱ ቀስ በቀስ እየጠፋባቸው እንደሆነ ሲናገሩ ሌሎች ደግሞ ባገኙት አጋጣቢ በዓሉን አክብረው እንደሚውሉ ለፓሪሷ ወኪላችን ሐይማኖት ጥሩነህ ገልፀውላታል። በተለይ በስደት ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በዓሉን እንዴት አከበሩት ሐይማኖት ጥሩነህ ገልፃልናለች።

ሮም የሚገኘው የዶይቸ ቬለ ወኪል ተክለ እዝጊ ገብረ እየሱስም እንዲሁ ፤ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ስደተኞች በዓሉን እንዴት እንደሚያከብሩ ከሮም ዘገባ ልኮልናል።

ሁሉንም ከዚህ በታች በድምፅ ያገኛሉ።

ልደት አበበ / ማንተጋፍቶት ስለሺ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ ዘገባዎች አሳይ