1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጋና አጠቃላይ ምርጫ

ቅዳሜ፣ ኅዳር 29 2005

በምዕራብ አፍሪቃዊቱ ሀገር ጋና በትናንቱ ዕለት ምክር ቤታዊ እና ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ተካሂዶዋል። በአፍሪቃ የዴሞክራሲ አርአያ ናት በምትባለው ጋና ውስጥ የተለያዩት የፖለቲካ ፓርቲዎች ለ 275 የምክር ቤት መንበሮች ይወዳደራሉ።

https://p.dw.com/p/16yKq
epa03499950 Ghanaians line up to vote in the presidential elections in the village of Kibi, Ghana, 07 December 2012. About 13.6 million people were expected to cast their ballots for Ghana's next president and for the 275 parliamentary candidates in Africa's cocoa and oil-producing state. The presidential race was expected to be a tight one between incumbent president John Dramani Mahama, of the National Democratic Congress (NDC), and his main opponent Nana Akufo-Addo, of the New Patriotic Party (NPP). Provisional election results are expected to be announced about 48 hours after polls close. If no candidate wins 50 per cent plus one of the votes, a run-off is to be held on 28 December 2012. EPA/LEGNAN KOULA
መራጭ ሕዝብምስል picture-alliance/dpa

ለከፍተኛው የሀገሪቱ ሥልጣን ስድስት ዕጩዎች በተወዳዳሪነት ቢቀርቡም፡ ዕድል አላቸው የሚባሉት ሁለት ተወዳዳሪዎች የብሄራዊው ዴሞክራቲክ ኮንግረስ መሪና የወቅቱ ፕሬዚደንት ጆን ድራማኒ ማሃማ፡ እንዲሁም የተቃውሞው የአዲሱ አርበኞች ፓርቲ መሪ ናና አኩፎ አዶ ናቸው። የቀድሞው የሀገሪቱ ፕሬዚደንት ጆን አታ ሚልስ ባለፈው ሐምሌ ድንገት ከሞቱ በኋላ በዚያን ወቅት ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩት ሥልጣኑን የያዙት ማሃማ በዚሁ ሥልጣን ለመቆየት ጠንካራ ፍላጎት ያሳዩ ሲሆን፡ ተፎካካሪያቸው እና እአአ በ 2008 ዓም በተካሄደው ምርጫ በጆን አታ ሚልስ በጠባብ የድምፅ ብልጫ የተሸነፉት ናና አኩፎ አዶ ዕድላቸውን ዘንድሮ እንደገና ሞክረዋል።
የብሄራዊው ዴሞክራቲክ ኮንግረስ እና የተቃውሞው የአዲሱ አርበኞች ፓርቲ፡ ሁለቱም በምክር ቤታዊው እና በፕሬዚደንታዊው ምርጫ ድል ለመቀዳጀት ይችሉ ዘንድ ባለፉት ወራት ጠንካራ የምርጫ ዘመቻ ነበር ያካሄዱት። በሁለተኛዋ ትልቋ የጋና ከተማ ኩማዚ የሚገኙት የአዲሱ አርበኞች ፓርቲ የወጣቶች ቡድን አስተባባሪ ሀቢቡ ሱዋላሂ ለምሳሌ ፓርቲያቸው ለድል ለማብቃት ያለፉትን ሦስት ወራት ያላሰለሰ የቅስቀሳ ስራ ማከናወናቸውን  ገልጸዋል። ሱዋላሂ በተለይ በከተማይቱ ዋነኛ የገበያ ቦታ በመዘዋወር ባለመደብሮች የብሄራዊ አርበኞች ፓርቲን እንዲመርጡ ሲያግባባ ነው የከረመው።
« በብሄራዊ አርበኞች ፓርቲ የሚመራ መንግሥት እንዲቋቋም ነው የምንፈልገው፤ ሕዝቡ የሚፈልገውን ያውቃሉና። ሥልጣን በምትይዝበት ጊዜ ሕዝቡን የሚጠቅም፡ ለምሳሌ፡ የጤና መድን ዋስትና ለሁሉም ተደራሽ ማድረግና ለወጣቱ የሥራ ቦታ መፍጠርን የመሳሰሉ ተግባራትን እውን ማድረግ ይኖርባሀል። »
የአዲሱ አርበኞች ፓርቲ ጠንካራ ሠፈር በምትባለው እና የአሻንቲ ሕዝብ በሚኖርባት ኩማዚ እና አካባቢዋ የፓርቲው ዕጩ ናና አኩፎ አዶ ከአራት ዓመት በፊት በተካሄደው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ 72 ከመቶ የመራጩን ድምጽ ነበር ያገኙት። በዘንድሮውም ምርጫ በዚሁ አካባቢ የብዙኃኑን ድምፅ ማግኘታቸው እንደማይቀር ነው የሚጠበቀው።  ይሁንና፡ በጠቅላላው የምርጫ ውጤት ላይ በ 30,000 የመራጭ ድምፅ ልዩነት በተፎካካሪያቸው ጆን አታ ሚልስ መሸነፋቸው ይታወሳል። በምርጫው ዘመቻ ወቅት ሁለቱም ተወዳዳሪዎች ማሀማኒ እና አዶ ተመሳሳይ አጀንዳ ይዘው ነበር የተንቀሳቀሱት። ምክንያቱም፡ ባለፉት ዓመታት የጋና ሕዝብ በዓለም ሦስተኛ የካካዎ  እና የነዳጅ ዘይት አምራች ከሆነችው የሀገሩ የተፈጥሮ ሀብት ገቢ ተጠቃሚ አልሆነም። በዚሁ ረገድ ገና ብዙ ማስተካከያ ሊደረግ እንደሚገባውና በሀገሪቱም አስፈላጊውን የማሻሻል ርምጃ የማነቃቃት የተሻለ ችሎታ እንዳላቸው ወቅታዊው ፕሬዚደንት ገልጸዋል።
« የመፀዳጃውን ዘርፍ በማስተካከሉ ረገድ ጠቃሚ ፖሊሲ አለመነደፉ እና ይህን የሚያዘጋጅ ጠንካራ ተቋም አልተገነባም። በሚቀጥለው ሣምንት ማብቂያ ላይ ያካባቢ ልማት ሚንስቴር አንድ ብሔራዊ የቆሻሻ ማስወገጃ እና የመፀዳጃ መርሀግብር ይፋ ያደርጋል። »
ትምህርት፡ ጤና ጥበቃ ፡ ብልፅግና የተሰኙትን ጉዳዮች በተመለከተ ሁለቱ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ዕጩዎች ሊያደርጉት በገቡት ቃል መካከል ብዙም ልዩነት አልታየም። ማሀማ እና አዶ ከሀገሪቱ የነዳጅ ዘይት እና የካካዎ ሽያጭ የሚገኘውን ግዙፍ ገቢ የትምህርቱን እና የጤናውን ዘርፍ ለማሻሻያ እንደሚጠቀሙበት ቃል ገብተዋል።  እርግጥ፡ ጋና በምዕራብ አፍሪቃ ካሉት ጎረቤቶችዋ በጉልህ በተሻለ ደረጃ ላይ ብትገኝም፡ አሁንም በመልማት ላይ ከሚገኙት ሀገራት መደዳ ነው የምትመደበው። 182 ሀገራትን የተመለከተው የተመድ የልማት ዕድገት ሠንጠረዥ እንደሚያሳይ፡ ይህችው የምዕራብ አፍሪቃ ሀገር 152 ኛ ደረጃ  ላይ ትገኛለች። በሀገሪቱ ሙስና አሁንም አሳሳቢ ጉዳይ እንደሆን ይገኛል። መንበሩን ጀርመን ያደረገው የሙስናን ደረጃ የሚመረምረው ድርጅት « ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል » 176 ሀገራትን አወዳድሮ ከጥቂት ቀናት በፊት ባወጣው ዓመታዊ ሠንጠረዡ፡ ጋና  64 ነጥቦችን በማግኘት 49 ደረጃ ላይ ትገኛለች።
ጋና በአፍሪቃ አስተማማኙ መረጋጋት የሰፈነባት ሀገር ናት። ባለፉት በርካታ ዓመታት ሥልጣኑን የሀገሪቱ አመራር በብሔራዊ ዴሞክራቲክ ኮንግረስ እና በአዲሱ የአርበኞች ፓርቲ መካከል በሰላማዊ መንገድ ሲሸጋገር ታይቶባታል ሲሉ በኩራት ይናገራሉ።
« ምርጫ ስናካሂድ የመጀመሪያችን አይደለም። ከአምስት የሚበልጡ ምርጫዎች ተካሂደዋል። እና፡ በርግጥ፡ ይህም ምርጫ ይሳካል፤ ። »
የትናንቱ አጠቃላይ ምርጫ አሸናፊ የሚታወቅበት ይፋ ውጤት በነገው ዕለት ይወጣል ተብሎ ይጠበቃል። ማሃማኒ እና አዶ የምርጫውን ውጤት በፀጋ እንደሚቀበሉ ከወዲሁ አስታውቀዋል። በምርጫው አንዱም ዕጩ 50% ካላገኘ እአአ የፊታችን ታህሳስ 28 የመለያው ምርጫ ይካሄዳል።

Kakaoplantage auf Sao Tome und Principe Schlagworte: Kakao, Plantage, Sao Tome, Principe, Unabhängigkeit Wer hat das Bild gemacht?: Marta Barroso Wann wurde das Bild gemacht?: Juni / Juli 2010 Wo wurde das Bild aufgenommen?: Sao Tome und Principe Bildbeschreibung: Bei welcher Gelegenheit / in welcher Situation wurde das Bild aufgenommen? Wer oder was ist auf dem Bild zu sehen? Auf der Kakaoplantage Rio do Ouro wird seit der Unabhängigkeit kaum noch Kakao angebaut.
የካካዎ ተክልምስል DW
mit den Orten Nkawkaw, Koforidua und der Hauptstadt Accra eingezeichnet
ምስል DW
Opposition presidential candidate Nana Akufo-Addo, center, looks on from the stage during his final campaign rally ahead of Friday's presidential election, in Accra, Ghana, Wednesday, Dec. 5, 2012. Far right is former Ghana President John Agyekum Kufuor. After five coups and decades of stagnation, the West African nation of 25 million is now a pacesetter for the continent's efforts to become democratic. Ghanaians will go to the polls on Friday to choose between four candidates, including President John Dramani Mahama, a former vice president who assumed the top post in July after the death of president John Atta Mills, and former foreign minister Akufo-Addo who lost the presidency by less than 1 percent in 2008.(Foto:Christian Thompson/AP/dapd)
የአዲሱ አርበኞች ፓርቲ መሪ ናና አኩፎ አዶምስል dapd
Ghanaian leader John Mahama speaks to supporters during the presidential rally of the ruling National Democratic Congress at Ashaiman, Greater Accra in Ghana on December 3, 2012. The presidential candidate of the ruling National Democratic Congress Mahama has intensified a campaign for his re-election shuttling between constituencies in different parts of the country to canvas for votes ahead of December 7 elections. AFP PHOTO/PIUS UTOMI EKPEI . (Photo credit should read PIUS UTOMI EKPEI/AFP/Getty Images)
ፕሬዚደንት ጆን ድራማኒ ማሃማምስል Getty Images

ዳንየል ፔልስ/አርያም ተክሌ

መሥፍን መኮንን
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ