የግራዚያኒ መታሰቢያና ተቃዉሞዉ
ረቡዕ፣ የካቲት 13 2005ማስታወቂያ
ለፋሽስት ኢጣሊያ የጦር መሪ ለማርሻል ሮዶልፎ ግራዚያኒ መታሰቢያ ቤተ-መዘክርና መናፈሻ መሰየሙት በመቃወም ዉጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን የሚያደርጉት ሠልፍና ጥያቄ እንደቀጠለ ነዉ። በግራዚያኒ የታዘዘዉ የፋሽት ኢጣሊያ ጦር በብዙ ሺሕ የሚቆጠር የአዲስ አበባና የአካባቢዋን ሕዝብ የጨፈጨፈበት ዕለት ትናንት ሲታሰብ፥ በሃያ-አምስት ከተሞች የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ተቃዉሟቸዉን በያሉበት አሰምተዋል።በየከተሞቹ የተሰበሰቡት ወይም አደባባይ የወጡት ኢትዮጵዉያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የኢጣሊያ መንግሥትና የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ለፋሽስቱ የጦር መሪ መታሰቢያ መቆሙን እንዲቃወሙ አቤት ብለዋል።ዋሽግተን ዲሲ የተደረገዉን ሠልፍ አበበ ፈለቀ ተከታትሎት ነበር። ሥለ ሠልፉ ሒደትና ዉጤት በስልክ ጠይቄዋለሁ።
አበበ ፈለቀ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ