1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የግብፅና የዩናይትድ ስቴትስ መሪዎች ዉይይት

ረቡዕ፣ ነሐሴ 13 2001

ሁለቱን ወገኖች ለመሸምገል የሚደረገዉን ጥረት ኦባማ «አበረታች» ሲሉት፥ ሙባረክ ግን «በመሠረታዊ» ጉዳዮች ላይ ዉይይት መጀመር አለበት ይላሉ።

https://p.dw.com/p/JEJk
ምስል AP

ካለፈዉ ቅዳሜ ጀምሮ ዩናይትድ ስቴትስን በመጎብኘት ላይ የሚገኙት የግብፅ ፕሬዝዳት ሆስኒ ሙባረክ ትናንት ከጋባዣቸዉ ከፕሬዝዳት ባራክ ኦባማ ጋር ተነጋግረዋል።የሁለቱ መሪዎች ዉይይት የኢራንን የኑክሌር መርሐ-ግብርና የሱዳንን ሁኔታ መነካካቱ ባይቀርም-ዋናዉ ትኩረት የፍልስጤም እስራኤሎች ሠላም ነዉ።ሁለቱን ወገኖች ለመሸምገል የሚደረገዉን ጥረት ኦባማ «አበረታች» ሲሉት፥ ሙባረክ ግን «በመሠረታዊ» ጉዳዮች ላይ ዉይይት መጀመር አለበት ይላሉ።አበበ ፈለቀ ከዋሽንግተን ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።

አበበ ፈለቀ /ነጋሽ መሀመድ

አርያም ተክሌ