1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጠ/ሚ መለስ ህልፈት እና የፓርቲዎች አስተያየት

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 15 2004

ኢትዮጵያዉ ጠቅላይ ሚኒስትር ከዚህ ዓለም በሞት መለየት ዛሬ በይፋ ከተገለፀ በኋላ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከዛሬ ጀምሮ ብሄራዊ ሃዘን ማወጁ ተገልጿል። ይህን የገለፁት የመንግስት ኢንፎርሜሽንና ኮሚዉኒኬሽን ሚኒስትር አቶ በረከት ስምኦን፤

https://p.dw.com/p/15ttg
አቶ መለስ ዜናዊምስል AP

በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመለከቱትም ስርዓተ ቀብሩ እስኪፈፀም ብሄራዊ ሃዘን ነዉ፤ ሰንደቅ ዓላማም ዝቅ ብሎ ይዉለበለባል። መካነ መቃብራቸዉ የት እንደሚሆን ግን አልተገለፀም። እንደዓለም ዓቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘገባ ከሆነ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አስከሬን ዛሬ ከቀትር በኋላ አዲስ አበባ ገብቷል።

በጠቅላይ ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊ የዜና እረፍት ላይ የተለያዩ አካላት፤ የአቶ መለስ ሞት፤ በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ አመራር ላይ የሚኖረውን ተፅዕኖ እየሰጡ ነው።

Äthiopien - verstorbender Premierminster Meles Zenawi mit Azeb Mesfin
ምስል dapd

ከፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ያነጋገርናቸው፤ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ኃይሉ ሻውል፣ የአንድነት ለዲሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ሰብሳቢ እና የምክር ቤት አባል-አቶ ግርማ ሰይፉ ፣ አቶ ሴኩ ቱሬ ጌታቸው ከህወሓት፣ በአሁኑ ሰዓት የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር -ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ ፣ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር -ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና የሰጡን አስተያየቶችን ማድመጥ ይቻላል።


ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

ልደት አበበ

ሸዋዬ ለገሠ
ነጋሽ መሀመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ