1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ከህዝብ እይታ መሰወር

ዓርብ፣ ነሐሴ 4 2004

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የጤንነት ይዞታና ያሉበት ሁኔታ አነጋጋሪ የሆነዉ በኢትዮጵያዉያን ዘንድ ብቻ አይደለም። ጉዳዩ በሀገር ዉስጥና በዉጭ በሚገኙ በርካታ የዲፕሎማሲዉ ማኅብረሰብ አባትም ጭምር መነጋገሪያ ስለመሆኑ ከየአቅጣጫዉ እየተገለፀ ነዉ።

https://p.dw.com/p/15nsD
ምስል picture-alliance/dpa

በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የታወቁ መፅሔቶችና ጋዜጦችም ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተዉ አቶ መለስ ዜናዊ የትናቸዉ በማለት እየጠየቁ፤ ስለጤንነታቸዉም ሆነ ስላሉበት ሁኔታ በመንግስት በኩል እስካሁን የተሰጠዉ መግለጫም የሚያረካ ሳይሆን ጥርጣሬዎችን የሚያጭር መሆኑን በመግለፅ ፅፈዉ አስነብበዋል። አንዳንዶቹ ዘገባዎች ሁኔታዉ በየዓመቱ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን ለመንግስታቸዉ የሚለግሱ ወገኖችንም ማሳሰቡን ነዉ ያመለከቱት።  

 ገበያዉ ንጉሤ

ሸዋዬ ለገሠ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ