1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጥራት ጥያቄ ያስነሳው ጭንብል በጀርመን

ሐሙስ፣ ሰኔ 3 2013

ጀርመን ውስጥ ደረጃውን ያልጠበቀ ነው በተባለ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ምክንያት የሀገሪቱ የጤና ሚኒስትር እየተወቀሱ ነው። በዚህም ምክንያት የጀርመን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቡንደስታኽ በዛሬው ዕለት በጉዳዩ ላይ ተነጋግሯል።

https://p.dw.com/p/3uilK
Deutschland Kabinettssitzung Coronavirus Jens Spahn
ምስል John Macdougall/AFP/Getty Images

ምክር ቤት አጣሪ ኮሚቴ እንዲሰየም ወስኗል

ጀርመን ውስጥ ደረጃውን ያልጠበቀ ነው በተባለ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ምክንያት የሀገሪቱ የጤና ሚኒስትር እየተወቀሱ ነው። ከቻይና በገፍ የተገዛው FFP2 የተሰኘው የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ በተለይ በኑሮ ደረጃቸው ዝቅ ላለው የኅብረተሰብ ክፍል እና ለአካል ጉዳተኞች ይሰጥ መባሉ ውዝግብ ቀስቅሷል። ሆኖም የሀገሪቱ የጤና ሚኒስትር የን ሽፓን ወቀሳውን በማጣጣል የተጠቀሰው የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ አስቀድሞ የጥራት ይዘቱ ተፈትሾ መገዛቱን ይናገራሉ። በዚህም ምክንያት የጀርመን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቡንደስታኽ በዛሬው ዕለቱ በጉዳዩ ላይ ተነጋግሮ አጣሪ ኮሚቴ እንዲቋቋም ወስኗል። ሽፓን ከሶሻል ዴሞክራት ጋር በመጣመር ሀገር የሚያስተዳድረው የመራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ፓርቲ የክርስቲያን ዴሞክራት አባል ሲሆኑ፤ ይኽ ውዝግብ በጥምረቱ መካከል ተጨማሪ የመነታረኪያ ምክንያት እንደሆነ ነው የሚነገረው።

ይልማ ኃይለ ሚካኤልን

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ