1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፋታህ ማዕከላዊ ኮሚቴ ምርጫ

ረቡዕ፣ ነሐሴ 6 2001

የፍልስጤማውያን ፕሬዚደንት ማህሙድ አባስ የሚመሩት የፋታህ ድርጅት በፓርቲው አመራር ላይ ከብዙ ጊዜ ወዲህ ሲጠበቅ የነበረውን ተሀድሶ አነቃቃ።

https://p.dw.com/p/J8FW
ምስል AP

ፓርቲው ባለፈው ሳምንት በቤተልሄም ከተማ ካለፉት ሀያ ዓመታት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ባካሄደው ጉባዔው ላይ ሀያ አንድ አባላት ከሚያጠቃልለው የማዕከላዊ ኮሚቴ መካከል ሁለት ሶስተኛውን በትናንቱ ዕለት የመረጠ ሲሆን መርጦዋል። ክሌመንስ ፈሬንኮተ እንደዘገበው፡ ብዙ ወጣት ተመራጮችን ባስገኘው ምርጫ ከተመረጡት መካከል በእስራኤል ወህኒ ቤት የሚገኙትና ፕሬዚደንት ማህሙድ አባስን የመተካት ዕድል አላቸው የሚባሉት የሀምሳ ዓመቱ ማርዋን ባርጉቲ ይገኙበታል።

ክሌመንስ ፈሬንኮተ/ይልማ ሀይለሚካኤል/ሸዋዬ ለገሠ