«የፌዴራል መንግሥት በአግባቡ እየደገፈን አይደለም»
ዓርብ፣ ግንቦት 14 2012ማስታወቂያ
የኮረና ተሕዋሲ ወረርሽኝን ለመግታት በሚደረግ ጥረት የትግራይ ክልላዊ መንግስት ከፌደራል መንግስት ተጨማሪ የበጀት፣ ሕክምና መሳሪያዎችና ሌሎች ድጋፎች እንደሚሻ ገለፀ፡፡ የትግራይ ክልል ኮምኒኬሽን ቢሮ ሐላፊ ወይዘሮ ሊያ ካሳ እንዳሉት እስካሁን የፌደራል መንግስት ለክልሉ ሲያደርግ የነበረው ድጋፍ አነስተኛ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የፌደራሉ መንግስት ባወጀው አስቸኳይ ግዜ አዋጅ ዙርያ የትግራይ ክልል መንግስት ግልፅነት እንደሚሻ ወይዘሮ ሊያ ጨምረው ገልጸዋል።