1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፕሬዚዳንት ኦባማ ዳግመኛ ጉብኝት በበርሊን

ሰኞ፣ ሰኔ 10 2005

የዩናይትድ እስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ፤ በጥቅምት ወር ማለቂያ ገደማ፤ 2001 ለመጀመሪያ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት እጩ ተወዳዳሪ ሆነው ከመቅረባቸው ጥቂት ወራት ቀደም ሲል በሐምሌ ፤ 2000 ዓ ም፤ በርሊንን ጎብኝተው እንደነበረ የሚታወስ ነው ።

https://p.dw.com/p/18rKi
Der designierte demokratische US-amerikanische Präsidentschaftskandidat Barack Obama (r) erhält am Donnerstag (24.07.2008) im Hotel Adlon in Berlin im Anschluss an ein Gespräch mit dem Regierenden Bürgermeister von Berlin, Klaus Wowereit (SPD), einen Bären aus Porzellan. Am Abend will Obama vor der Siegessäule im Tiergarten eine Rede zu seinen Vorstellungen über die künftige transatlantische Zusammenarbeit halten. Foto: Michael Kappeler dpa/lbn +++(c) dpa - Report+++
ምስል picture-alliance/dpa

ያኔ፤ ከ 200,000 የማያንስ ህዝብ ፣ በጋለ ስሜትና አድናቆት አቀባበል በማድረግ ንግግራቸው ማዳመጡ የሚታወስ ነው። ኦባማ ፤ ነገ ማታ በርሊን ገብተው ፤ በማግሥቱ በብራንደንቡርግ በር ንግግር የሚያሰሙ ሲሆን ፤ እንደያኔው ህዝቡ በጋለ ስሜት ያዳምጠቸዋል ተብሎ እንደማይታሰብ ነው የሚነገረው። ስለአሁኑ ጉብኝት ዓላማ ፣ የሁለቱ መንግሥታት መሪዎች ፣ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማና የጀርመን መራኀተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ስለሚያተኩሩባቸው ዐበይት ጉዳዮች ፣የበርሊኑን ዘጋቢአችንን ይልማ ኃይለ ሚካኤልን በስልክ አነጋግሬው ነበር።

ይልማ ኃይለ ሚካኤል

ተክሌ የኋላ

አርያም ተክሌ