የ«DW» ልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ
ሰኞ፣ መጋቢት 16 2011ማስታወቂያ
ከፍተኛ አመራሮች ያካተተው የ«DW» ልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ኹኔታ ላይ ከመገናኛ ብዙኃን እና የሲቪክ ማኅበራት መሪዎች ጋር ተወያዩ። ውይይቱን ያዘጋጁት በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ብሪታ ቫግነር ናቸው። በውይይቱ የ«DW» ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፒተር ሉምቡርግ፣ የአፍሪካ ክፍል ተጠሪ ክላውስ ሽቴከር እና የአማርኛዉ ክፍል ተጠሪ ሉድገር ሻዶምስኪ ታድመዋል። የአማራጭ የኖቤል ሽልማት አሸናፊዋ የትነበርሽ ንጉሴ፣ የሶል ሪቤልስ መስራቿ ቤተልሔም ጥላሁን፣ ጦማሪ እና የሰብዓዊ መብት አቀንቃኙ በፍቃዱ ኃይሉ ተገኝተዋል።
እሸቴ በቀለ
አዜብ ታደሰ