ዩኤስ በሱዳን ላይ የጣለችው አዲሱ ማዕቀብ25 ግንቦት 1999ቅዳሜ፣ ግንቦት 25 1999የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚደንት ጆርጅ ዳብልዩ ቡሽ በዳርፉር በቀጠለው ውዝግብ ሰበብ በሱዳን ላይ ከጥቂት ቀናት በፊት አዲስ ማዕቀብ ጣሉ። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት፡ ሂውማን ራይትስ ዎች ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ስቲቭ ክሮሾው ይህንኑ የዩኤስ ርምጃ መልካም ሲሉ ቢያሞግሱም፡ ለሱዳን መንግሥት ግልፁን መልዕክት የሚያስተላልፈው የተመድ የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት የሚያሳርፈው ማዕቀብ መሆኑን በማመልከት፡ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጠንካራ ርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አhttps://p.dw.com/p/E0azየዳርፉር ስደተኞች መጠለያ ሠፈርምስል APማስታወቂያሰምተዋል።