1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዶ/ር ነጋሶ በተቃውሞ የፖለቲካ ትግል

ሰኞ፣ ሚያዝያ 21 2011

ኢትዮጵያን ለሰባት ዓመታት በፕሬዝዳንትነት ያገለገሉት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ባለፈው ሐሙስ ቅዳሜ  በጀርመን ፍራንክፈርት በ76 ዓመታቸው ማረፋቸው ይታወሳል። የቀድሞው ፕሬዝዳንት በተቃውሞ የፖለቲካ ትግል ውስጥ የነበራቸው እንስቃሴ ምን ይመስል ነበር?

https://p.dw.com/p/3HfGq
Negasso Gidada ehemaliger Präsident von Äthiopien
ምስል DW/Y. Gebregziabher

ዶ/ር ነጋሶ በተቃውሞ የፖለቲካ ትግል

በኦሮሚያ ክልል በቄለም ወለጋ ደምቢዶሎ ከቾ በተባለ ቦታ ጳጉሜ 3 ቀን 1935 ዓ.ም የተወለዱት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ሚና ከነበራቸው ግለሰቦች መካከል አንዱ ነበሩ። አምስት አስርት አመታት ገደማ በዘለቀ የፖለቲካ ሕይወታቸው ኢትዮጵያን በፕሬዝዳትነት ከመምራት ባሻገር የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)፣ የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) እና የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ከፍተኛ አመራር ሆነው አገልግለዋል። 

ከደርግ ውድቀት በኋላ በ1983 ዓ.ም. ከተማሩበት እና ረጅም ዓመታት ከቆዩበት ጀርመን ሀገር ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱት ዶ/ር ነጋሶ  በሽግግር መንግሥቱ ወቅት የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ እና በኋላም የማስታወቂያ ሚኒስትር ሆነው ሰርተዋል።

Negasso Gidada ehemaliger Präsident von Äthiopien
ምስል DW/Y. Gebregziabher

ከ1987 እስከ 1994 ዓ.ም. መጀመሪያ ድረስ ኢትዮጵያን በፕሬዘዳንትነት የመሩት ዶ/ር ነጋሶ ከኦህዴድ ኢሕአዴግ አባልነታቸው በገዛ ፈቃዳቸው የለቀቁት በሰኔ 15 ቀን 1993 ዓ.ም. ነው። በግንቦት 1997 ዓ.ም. በተደረገው የኢትዮጵያ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው ተወዳድረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫን አሸንፈዋል። የቀድሞው ፕሬዝዳንት የተወካዮች ምክር ቤት ቆይታ እና ከመንግስት መዋቅር የለቀቁበትን ወቅት ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና መለስ ብለው ያስታውሳሉ። በአንድነት ፓርቲው ውስጥ አብረዋቸው የሰሩት አቶ አስራት ጣሴም ስለ ዶ/ር ነጋሶ የሚሉት አላቸው።    

ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ። 

ዩሃንስ ገብረ እግዚያብሔር

ተስፋለም ወልደየስ 

እሸቴ በቀለ