1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጀርመናውያን ወጣቶች እና የሥራ አጥነቱ ችግር

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 27 1997

ጀርመን ባለፉት ስድስት ዓመታት ውስጥ በሥራ ገበያውም ሆነ በኤኮኖሚያዊ ዕድገቱ ዘርፍ ጥሩ ውጤት እንዳላስመዘገበች ተገለፀ።

https://p.dw.com/p/E0el

ይህንን መግለጫ ያወጣው ከጥቂት ጊዜ በፊት ሀያ አንድ ኢንዱስትሪ መንግሥታትን በማወዳደር የሕዝብ አስተያየት መመዘኛ መዘርዝር ያካሄደው የጀርመናውያኑ የቤርትልስማን ተቋም ነው። በተቋሙ ዘገባ መሠረት፡ ጀርመን አሁንም የመጨረሻውን ቦታ እንደያዘች ትገኛለች። በስጳኝ እና በግሪክ የሚታየው የሥራ አጦች አሀዝ ብቻ ነው ከጀርመን ከፍ ብሎ የሚገኘው። በተለይ የወጣቱ ሥራ አጥነት ጉዳይ አሳሳቢ እየሆነ መጥቶዋል። በአሁኑ ጊዜ ከአምስት መቶ ሺህ የሚበልጡ ጀርመናውያን ወጣቶች ሥራ የላቸውም።