ጀርመን ከባራክ ኦባማ ብዙ ትጠብቃለች12 ጥር 2001ማክሰኞ፣ ጥር 12 2001ከጥቂት ሠዓታት በኋላ፤ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸው በተገኙበት፤ የአርባ ሰባት ዓመቱ ጎልማሳ የኢሊዮኑ ሴናተር ባራክ ኦባማ የ US አሜሪካ አርባ አራተኛው ፕሬዚዳንት ተብለው ይሰየማሉ።https://p.dw.com/p/Gcrvዲሞክራቱ ባራክ ኦባማምስል APማስታወቂያአሜሪካ ከፕሬዚዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ በኋላ አንድም ፕሬዚዳንቷ እንዲህ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭው ዓለም እጅግ ተወዳጅ ሆኖላት አያውቅም። ጥቁር አሜሪካዊው የመጀመሪያ ፕሬዚዳንት ሆነው ዛሬ ማታ ቃለ መሃላ በሚፈፅሙት ባራክ ኦባማ በርካታ የጀርመን ፖለቲከኞችም ደስተኛ መሆናቸው ታውቓል። ለመሆኑ ጀርመን ከአዲሱ የአሜሪካን አስተዳደር ምን ትጠብቃለች?