1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጅጅጋ የበዓል ዝግጅትና ወከባ

ማክሰኞ፣ ጥቅምት 26 2006

ጸጥታ አጠባበቁ በተለይ በእጅጉ መጠናከሩም ተሰምቷል። ከዚሁ የተነሳ ኣንዳንድ የከተማይቱ ኗሪዎች ፍተሻው እና ወከባው በዝቶብናል ሲሉም ያማርራሉ። አንድ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የጅጅጋ ከተማ ኗሪ ደግሞ የተመቱ እና የተዘረፉም አሉ ይላሉ።የክልሉ የማስታወቂያ እና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ መሐመድ ጎሬ ግን ይህ መሰረተ ቢስ ነው ሲሉ አስተባብሏል።

https://p.dw.com/p/1ACGi
***Für mögliche Ergänzungen der Karte, wie z.B. andere Sprachen, zusätzliche Orte oder Markierungskreuz, wenden Sie sich bitte an infografik@dw-world.de (-2566), Außerhalb der Bürozeiten an bilder@dw-world.de (-2555).*** DW-Grafik: Per Sander 2011_03_10_Laender_Prio_A_B

በየዓመቱ በዚህ ወር መጨረሻ የሚከበረረው የኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰቦች ቀን የዘንድሮው በሶማሌ ክልል ሊከበበር ዝግጅቱ እየተጠናቀቀ መሆኑ ተነገረ።በተለይም የጸጥታው ቁጥጥር እጅግ የተጠናከረ ከመሆኑ የተነሳ አንዳንድ የጅጅጋ ከተማ ኗሪዎች ወከባ በዝቶብናል ሲሉ ያማርራሉ።በክልሉ የተረጋጋ ሰላም መኖሩን የገለጸው የክልሉ መንግስት ግን የተባለውን ቅሬታ መሰረተ ቢስ ነው ሲል አስተባብሏል።ከኢትዮጵያ መንግስት አንጻር ነፍጥ የመዘዘው የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር ONLF በክልሉ በመንግስት ወታደሮች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት እየሰነዘርኩ ነው ሲል በተደጋጋሚ መግለጹ ይታወሳል።


የብሄር ብሄረ ሰቦች ቀን በኢትዮጵያ መከበር የጀመረው እየተሰራበት ያለው የኢትዮጵያ ህገመንግስት የጸደቀበትን ወርና ዕለት መሰረት አድርጎ ሲሆን ዓላማውም የመንግስት ባስልጣናት እንደሚያስተዋውቁት ከ80 በላይ ብሄረሰቦች በሚገኙባት ኢትዮጵያ ህዝቦች እርስ በእርሳቸው ይበልጥ እንዲተዋወቁ ልምድ እንዲለዋወጡ በእኩልነት ላይ ለተመሰረተ አንድነትና የጋራ ልማት ቃላቸውን የሚያድሱበት አጋጣሚ ነው።
አከባበሩም በየዓመቱ በተለያዩ ክልሎች እየተዘዋወረ ሲሆን የዘንድሮው ደግሞ የሚከበረው የሶማሌ ክልላዊ መንግስት መቀመጫ በሆነችው ጅጅጋ ከተማ ነው። ከአዲስ አበባ በስተ ምስራቅ 655 ኪ ሜ እና ከሐረር ደግሞ 130 ኪ ሜ ላይ የምትገኘው ጅጅጋ ከየክልሉ የሚመጡ እንግዶቿን ለማስተናገድ ዝግጅት የጀመረችው ከወር በፊት መሆኑ ታውቋል። የጸጥታ አጠባበቁ በተለይ በእጅጉ መጠናከሩም ተሰምቷል። ከዚሁ የተነሳ ኣንዳንድ የከተማይቱ ኗሪዎች ፍተሻው እና ወከባው በዝቶብናል ሲሉም ያማርራሉ። አንድ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የጅጅጋ ከተማ ኗሪ ደግሞ የተመቱ እና የተዘረፉም አሉ ይላሉ።

የክልሉ የማስታወቂያ እና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ መሐመድ ጎሬ ግን ይህ መሰረተ ቢስ አሉባልታ ነው ሲሉ አስተባብሏል።

የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ዘንድሮ በሶማሌ ክልል መከበሩ ያለምክኒያት ኣይደለም የሚሉ ወገኖችም ኣሉ። ምክኒያቱ ደግሞ በእነዚህ ወገኖች መግለጫ መሰረት በክልሉ ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረውን ኣለመረጋጋት መቆጣጠር የተሳነው የኢትዮጵያ መንግስት ጅጅጋ ላይ የብሔር ብሔረሰቦች ቀንን በማክበር በክልሉ ሰላም የሰፈነ ኣስመስሎ ለፕሮፓጋንዳ ሊጠቀምበት ኣስቦ ነው።
የክልሉ መንግስት ቃል ዓቀባይ አቶ መሐመድ ጎሬ ግን ይህንን ኣይቀበሉትም።

ጸጥታን በተመለከተ መንግስት በአካባቢው ሰላም መስፈኑን ቢናገርም ሸማቂው የኦጋዴን ነጻ ኣውጪ ግንባር ONLF በበኩሉ በመንግስት ወታደሮች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት እየሰነዘረ መሆኑን ሲገልጽ ቆይቷል። የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ መሐመድ ጎሬ እንዲያውም ONLF ብሎ ነገር የለም ካለም የሚገኘው በውጪ እንጂ በክልላችን ኣይደለም ባይ ናቸው።

በኢትዮጵያ ከኦሮሚያ ለጥቆ በቆዳ ስፋቱ በሁለተኛነት የሚጠቀሰው የሶማሌ ክልል 400 ሺህ ስኩዌር ኪ,ሜ ኃህል ስፋትም አለው። የህዝብ ብዛቱ ከ5 እስከ 6 ሚሊየን ይገመታል። በረኃማነት ቢያጠቃውም ክልሉ ከፍተኛ የተፈጥሮ ሀብት እንዳለው ይታመናል።

ጂዓፈር ዓሊ

ሸዋዬ ለገሠ



An ethnic Somali woman herds goats outside the town of Gode in the Ogaden region of eastern Ethiopia in January 2006. Journalists have been barred from the remote, isolated Ogaden region for much of 2007 as the Ethiopian military carries out a shadowy military campaign against a separatist rebel group known as the Ogaden National Liberation Front, or ONLF. Refugees and human rights groups charge the Ethiopian military with terrorizing and killing and civilians and forcibly recruiting villagers to fight the rebels, charges that the government denies. Foto: Shashank Bengali/MCT /Landov +++(c) dpa - Report+++
ምስል picture alliance/dpa
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ