1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ግብፅ ተቃዉሞ ከሙባረክ እስከ ሙርሲ

ዓርብ፣ ጥር 17 2005

ተሕሪር፥ ነፃነት አደባባይ፥ የሕዝባዊ አመፅ አብነት።ሠሞኑን ዳግም በሕዝባዊ አመፁ ተምሳሌት «ያሸበረቀበት»፥ በግጭት የተተራመሰበት ሠበብ ምክንያት ሁለት ነዉ።የሕዝባዊዉ ቀጣ ሁለተኛ ዓመት ዝክር-አንድ፥የፕሬዝዳት መሐመድ ሙርሲን አስተዳደርን መቃወም-ሁለት።

https://p.dw.com/p/17RPx
Protesters opposing Egyptian President Mohamed Mursi demonstrate at Tahrir Square in Cairo January 25, 2013. Hundreds of youths fought Egyptian police in Cairo on Friday on the second anniversary of the revolt that toppled Hosni Mubarak and brought the election of an Islamist president who protesters accuse of riding roughshod over the new democracy. Opponents of Mursi and his Muslim Brotherhood allies began massing in Cairo's Tahrir Square to revive the demands of a revolution they say has been betrayed by Islamists. REUTERS/Amr Abdallah Dalsh (EGYPT - Tags: POLITICS CIVIL UNREST)
Ägypten Kairo Demonstrationen am zweiten Jahrestag der Revolution 25. Januar 2013ምስል Reuters

የግብፅ ሕዝብ የፕሬዝዳት ሆስኒ ሙባረክን አምባገነናዊ ሥርዓት በመቃወም ታላቅ ሕዝባዊ ሠልፍ የጀመረበት ሁለተኛ ዓመት ዛሬ ተከብሯል።ግብፆች «የቁጣ ዕለት» ባሉት በዚያ በጎርጎሮሳዉያኑ ጥር 25 ቀን 2011 የጀመሩት የአደባባይ ትግል ከሰላሳ-ዓመት በላይ የፀናዉን ጨቋኝ ሥርዓት በገረሠሠ ድል ተጠናቅቋል።ሠልፍ ተቃዉሞዉ ግን ደረጃና ዓለማዉ ይለያይ እንጂ ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ።ባለፉት ሁለት ዓመታት የተቃዉሞ ማዕከል ከሆነዉ ከካይሮዉ ተሕሪር አደባባይ ያልተለየዉ ወጣት ኢብራሒም ከንደሪያን እንደሚለዉ አብዮቱ እንደቀጠለ ነዉ።የዶቸ ቬለዉ ማቲያስ ዛይለር ወጣት ኢብራሒምን አነጋግሮ ያዘጋጀዉን ዘገባ ነጋሽ መሐመድ አጠናቅሮታል።

ያ! የታላቅ ሕዝባዊ አብዮት፥ ትልቅ ማዕከል፥ ያ! ሕዝብ ካበረ የታንክ፥ መድፍ፥ የመትረየስ ጠመንጃ ጋጋታ እንደባይበግረዉ የተመሠከረበት አደባባይ መሰንበቻዉንም ዝግ ነዉ። በእሾሐማ ሾቦ ታጥሯል።አሸዋ የተሞሉ የላስቲክ ከረጢቶች ተደርድረዉበታል።ድንኳኖች፥ ነጫጭ ድንኳኖች ተተክለዉበታል።

ተሕሪር፥ ነፃነት አደባባይ፥ የሕዝባዊ አመፅ አብነት።ሠሞኑን ዳግም በሕዝባዊ አመፁ ተምሳሌት «ያሸበረቀበት»፥ በግጭት የተተራመሰበት ሠበብ ምክንያት ሁለት ነዉ።የሕዝባዊዉ ቀጣ ሁለተኛ ዓመት ዝክር-አንድ፥የፕሬዝዳት መሐመድ ሙርሲን አስተዳደርን መቃወም-ሁለት።

የሐያ-ስድስት ዓመቱ ወጣት ኢብራሒም ከንደሪያን ከአሌሳንደሪያ ካይሮ-የገባዉ ተሕሪር በሕዝባዊዉ ቁጣ መንተክተክ በመጀመረ- በሳልስቱ ነበር።ጥር-ሃያ ሥምንት ሁለት ሺሕ አሥራ-አንድ እንደ ጎሮጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር።ከያኔ-እስካሁን ከተሕሪር አደባባይ አልተለየም።ያኔ-በተቃዉሞ ሠልፈኛዉ ላይ የተፈፀመዉን ግፍ የዛሬ ከሚሆነዉ እኩል ያስታዉሰዋል፥-ወጣቱ።

«ፖሊሶቹ ማድረግ የሚችሉትን ሁሉ በሕዝቡ ላይ አድርገዋል።የፕላስቲክ ጥይት ተኩሰዋል።አሠለቃሽ ጢስ ረጭተዋል።ገዳይ ጥይት ተኩሰዋል።ሌላዉ ቀርቶ መኪኖቻቸዉን በሰልፈኛዉ ላይ ነድተዋል።»

ወጣቱ እያየ ሁለት ሠልፈኞች በፖሊስ መኪኖች ተደፈለቁ።በመቶ የሚቆጠሩ የእድሜ አቾቹ ተገደሉ።ሕዝባዊ ቁጣዉ ግን ናረ-እንጂ አልረገበም።አምባገነኑ ሥርዓት ተገረሠሠ-እንጂ አልቀጠለም።የካቲት አሥራ-አንድ።የሙባረክ ሥርዓት ፍፃሜ ታወጀ።ታላቅ ሕዝባዊ ድል።

epa02730603 Egyptians hold Egyptian and Palestinian flags and shout slogans during an 'unity rally' in Tahrir Square Cairo, Egypt, 13 May 2011. According to media sources, about thousands of Egyptians gathered in central Cairo's on 13 May to take part in a Unity Rally, following clashes between Muslims and Christian that left 13 people dead earlier this week, major political groups have called on Egyptians to participate in a million-strong rally in a show of unity and solidarity, and have demanded the prosecution of those instigating religious violence. The military council blamed remnants of Mubarak's regime for inciting the unrest in a bid to cause chaos in the country. EPA/KHALED ELFIQI
ተቃዉሞ-ሙባረክንምስል picture-alliance/dpa

#ሙባረክን የተኩት ወታደራዊ ጄኔራሎች ድሉን ከሕዝቡ እንዳይነጥቁ፥ ሕዝባዊ አብዮቱን ለራሳቸዉ ጥቅም እንዳያዉሉት ለመከላከል አብዮተኛዉ ለሌላ፥ ሠልፍ፥ ለሌላ ትግል መታደም፥ ሌላ መስዋዕትነት መክፈል ግድ ነበረበት።እነ ኢብራሒም አዲሱን አገዛዝ-ባዲስ እልሕ ሲጋፈጡ ሌሎች ብዙ መቶ አጋሮቻቸዉን አጡ።እሱ አልሞትም። ከሞት በመለስ ያለዉን ግፍ ግን ቀመሳት።ተሕሪር አደባባይ ተያዘ። እስር ቤት ተወረወረ።

«ደበደቡን፥ በጣም ደበደቡን።ክንዴን ሠበሩት።አቅሌን እስክስት ድረስ ገረፉኝ።ሌሎቹ መጡና ዳግም እንደምደበደብ ምናልባትም እንደምገደል ሲዝቱብኝ አቅሌን ገዛሁ።»

ሕዝባዊዉ አብዮት ግን ማርሻል ተንታዊንም ከቋመጡለት ወንበር አሽቀነጠራቸዉ።መርጫ መደረጉ፥ ተንታዊ የመሯቸዉ ጄኔራሎች ከሥልጣን መወገዳቸዉ በርግጥ ታላቅ ለዉጥ፥ ዳግማዊ ታላቅ ድልም ነዉ።በምርጫ ሥልጣን የያዙት ፕሬዝዳት መሐመድ ሙርሲና የቀድሞ ፓርቲያቸዉ ሙስሊም ወንድማማቾች ግን ለአብዮተኛዉ ጥያቄ ተገቢዉን መልስ አልሰጡም።እንዲያዉም ኢብራሒም እንደሚለዉ ሸሪዓ-ቀመስ ሕገ-መንግሥት አስፀድቀዉ ሕዝቡን ከፋፍለዉታል።የችግረኛዉን ሕዝብ ኑሮም ይበልጥ አክፍተዉበታል።

«ምንም የለወጡት ነገር የለም።ማንንም አይሰሙም።ሰዎች እየተቸገሩ፥ እየሞቱም ነዉ።ሰዉ መብላትና መኖር ይፈልጋል።»

አንድ-ተስፋ ግን አለዉ-ኢብራሒም።የሕዝቡ ችግር እየበረታ፥ እየጠከረ ሲሔድ፥ ብሶት በሚወልደዉ ምሬት-ሙስሊም ወንድማማቾችን ልክ-እንደ ሙባረክ ሁሉ ከፋችሁኝ-ከረፋችሁን፥ በቃችሁኝ ይላል የሚል-የእምነት ያክል የጠነከረ-ተስፋ።

«ጥሩዉ ነገር (,ሙስሊም ወንድማማቾ) እራሳቸዉ ወደ ዉድቀት መጓዛቸዉ ነዉ።ሙባራክ በራሳቸዉ ጥፋት እንደጠፉ ሁሉ እነዚሕም የሚወድቁበትን ጥፋት-እየፈፀሙ ነዉ።ይሕ አወንታዊ ነዉ።እንደሚመስለኝ አሁን አብዮቱን የሚመራ (ሐይል) የሚፈለግበት ወቅት ነዉ።»

አብዮቱ መሪ-ማግኘት ማጣቱ ላሁኑ አለየም።የሙርሲን አስተዳደር ከመቃወም ጋር የታላቁን ቁጣ-ሁለተኛ ዓመት ለመዘከር ተሕሪር አደባባይ የተሰለፈዉ ሕዝብ ግን ዘንድሮም፥ ለዉጥ እየጠየቀ፥ ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር እየተጋጨም ነዉ።

ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሠ








epa02730598 Egyptian protesters display a giant flag representing al Arabic countries during a 'unity rally' in Tahrir Square, Cairo, Egypt, 13 May 2011. According to media sources, about thousands of Egyptians gathered in central Cairo's on 13 May to take part in a Unity Rally, following clashes between Muslims and Christian that left 13 people dead earlier this week, major political groups have called on Egyptians to participate in a million-strong rally in a show of unity and solidarity, and have demanded the prosecution of those instigating religious violence. The military council blamed remnants of Mubarak's regime for inciting the unrest in a bid to cause chaos in the country. EPA/KHALED ELFIQI +++(c) dpa - Bildfunk+++
ተቃዉሞ-ጄኔራሎቹንምስል picture-alliance/dpa
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ