1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ግጭትና ዉጊያ ያልራቃት የመን

ረቡዕ፣ ጥቅምት 5 2007

በአንድ ሳምንት ዉስጥ ሁለት ጠቅላይ ሚኒስትሮች የተለዋወጡባት የመን ዛሬም የተረጋጋች አትመስልም። ከሰንዓ የሚወጡ የተለያዩ የዜና ወኪሎች ዘገባ እንደሚለዉ በሁቲ አማፅያንና በአልቃይዳ ታጣቂዎች መካከል የተካሄደዉ ዉጊያ ቢያንስ የ12 ሰዎችን ህይወት አጥፍቷል።

https://p.dw.com/p/1DW5y
Jemen Regierungschef Khaled Bahah ARCHIVBILD
ምስል Reuters/Khaled Abdullah

እንደዘገባዎቹ በወታደራዊ እንቅስቃሴያቸዉ በሀገሪቱ ማዕከላዊ መንግሥት ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደራቸዉ የሚታየዉ ሁለቱም ታጣቂ ኃይሎች ወደዉጊያ የገቡት የሚቆጣጠሩትን አካባቢ ለማስፋት ባደረጉት ሙከራ ነዉ። በተኩስ ልዉዉጡም ከአማፅያኑ አምስት፤ ከአልቃይዳ ታጣቂዎች ወገን ስድስት መገደላቸዉን ያመለከተዉ ዘገባ ቀሪዎቹ ሲቪሎች መሆናቸዉንም ገልጿል። አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰኞ ዕለት የተሰየመላት የመን ከሁለት ዓመት ከዘለቀዉ አለመረጋጋት ትላቀቅ ይሆን? ሰንዓ የሚገኘዉን ግሩም ተክለኃይማኖትን በስልክ ስለወቅታዊዉ የየመን ሁኔታ አነጋግሬዋለሁ፤

ግሩም ተክለሃይማኖት

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ