1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ከቦንጋ ነዋሪዎች ጋር ተወያዩ

ሰኞ፣ መስከረም 5 2012

የሸካ ሕዝብ የክልል እንሁን ጥያቄዉን በሰላማዊ መንገድ ማቅረቡ እንደሚያደንቁ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ትናንት በካፋ ሸካ ከሃገር ሽማግሌዎች እና ነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ዉይይት ላይ ነዉ ።

https://p.dw.com/p/3PfrJ
Äthiopien Premierminister Abiy Ahmed in Bonga
ምስል DW/Y. G/Egziabher

የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች እንደሚፈቱ ቃል ገብተዋል

የሸካ ሕዝብ የክልል እንሁን ጥያቄዉን በሰላማዊ መንገድ ማቅረቡ እንደሚያደንቁ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ትናንት በካፋ ሸካ  ከሃገር ሽማግሌዎች እና ነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ዉይይት ላይ ነዉ ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀረቡት የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ከመንግሥታቸዉ ጋር ተመካክረዉ እንደሚፈቱም ቃል ገብተዋል። በእለቱ ክልል ኃላፊዎች በተጨማሪ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸዉ፤  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እና የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ለማ መገርሳ ተገኝተዉ ነበር። ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ወደ ቦንጋ የተጓዘዉ ወኪላችን ዮኃንስ ገብረግዚአብሔር ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል። 

ዮኃንስ ገብረግዚአብሔር

አዜብ ታደሰ

ኂሩት መለሰ