1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጠፉ የተባሉት የኮንደሚኒየም ሕንጻዎች

ሰኞ፣ ግንቦት 8 2008

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ታቅደዉ ያልተሠሩ ቤቶች መኖራቸዉን ለምክር ቤቱ ጠቁሟል ።

https://p.dw.com/p/1IokB
Bezahlbarer Wohnraum wird knapp in Addis Abeba
ምስል DW/Y. Gebere Gziabeher

[No title]


የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቤቶችና የከተማ ልማት ሚኒስቴር የሥራ አፈፃፀም ዝርዝር ዘገባ ባደመጠበት ወቅት ጠፉ እየተባለ ስለሚነገርላቸዉ የኮንደሚኒየም ቤቶች የሚኒስቴር መሥርያ ቤቱ አጣርቶ እንዲያቀርብ መጠየቁ ተሰምቷል። ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ታቅደዉ ያልተሠሩ መኖራቸዉን ለምክር ቤቱ ቢጠቁምም፤ ጠፋ የተባሎት የኮንደሚኒየም ቤቶች ጉዳይ በተለያዩ ማኅበራዊ መገናኛ ገጾች የመነጋገርያ ርእስ ሆኗል። ጉዳዩን ጠቅሶ የአዲስ አበባ የቤቶችና የልማት አስተዳደር ቢሮን ያነጋገረዉ የአዲስ አበባዉ ዘጋብያችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር የሰመጠም፣ የተሰወረም ሕንፃ እንደሌለ መስሪያ ቤቱ መግለጹን በላከልን ዘገባ ጠቅሶአል።


ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር


አዜብ ታደሰ

ሸዋዬ ለገሠ