ጣምራ የሥነ ተዋልዶ ጤናና ልማት ድርጅት
ዓርብ፣ ነሐሴ 17 2005ማስታወቂያ
ከመሥራቾቹ አንዱ ብሩክ ይርጋለም ይባላል። የሚኖረው ተወልዶ ባደገበት ሻሸመኔ ከተማ ነው። በአሁኑ ሰዓት «ጣምራ የስነ ተዋልዶ ጤናና ልማት ድርጅት» ውስጥ የፕሮግራም አስተባባሪ ሆኖ ያገለግላል።
በሻሸመኔ ከተማ እያዝናኑ ማስተማር በሚል ፕሮግራማችን እንታወቃለን የሚለው ብሩክ፤ በስነ ጹሑፍ፣ ቲያትር ሙዚቃ እና ውዝዋዜ ዘርፍ ስር የሚካፈሉት ወጣቶች ትልቅ ቦታ ላይ ሲደርሱ መመልከታቸውን አይተናል ይላል። በ «ጣምራ የስነ ተዋልዶ ጤናና ልማት ድርጅት» ስር ያሉት ወጣቶች አብዛኞቹ በጎ ፍቃደኞች ናቸው።
«ጣምራ የስነ ተዋልዶ ጤናና ልማት ድርጅት» ለዚህ ስኬት ከማሕበረሰቡ ፣ ከመንግሥትም ይሁን ከተለያዩ መንግሥታዊ ያልሆኑ የውጭ በጎ አድራጎት ድርጅቶች ድጋፍ እና እውቅና ማግኘቱን ብሩክ ሳይገልፅ አላለፈም። በሻሸመኔ ከተማ የመጀመሪያውን የወጣት ማዕከል የመሠረቱት ወጣቶች በከተማቸው ሌሎች የወጣት ማዕከላት እንዲገነቡም አርአያ ለመሆን ችለዋል።
ብሩክ ስለ ድርጅቱ አጀማመር እና እንቅስቃሴ የገለፀልንን ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።
ልደት አበበ
ተክሌ የኋላ