1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጥንታዊ የብራና ጽሑፎች ጥናት በጀርመን

ሐሙስ፣ መስከረም 23 2006

ጀርመን የኢትዮጵያ ባህል ቋንቋ ጥናት በአዉሮጳ እንዲጀመር ያደረገች የመጀመርያዋ አዉሮጳዊት ሀገር መሆንዋ ይታወቃል።

https://p.dw.com/p/19tCA
Bild: Älteste äthiopische Bibelhandschrift - ist eine Silbenschrift; sie wird im Gegensatz zu den anderen semitischen Schriften von links nach rechts geschrieben. Titel: Die Forschungsstelle Äthiopistik der Universität Hamburg ist für die Aufgabe der Wahrung bedrohter äthiopischer Handschriften wie prädestiniert, weil sie seit langem Quellensicherung in Äthiopien betreibt und sich einen Namen gemacht hat in der Erforschung der Kulturgeschichte des Landes. 1968 wurde in Hamburg deutschlandweit der erste Lehrstuhl für Äthipistik eingerichtet.
ምስል DW/ A.T.Hahn

በሀንቡርግ ዩንበርስቲ የሚገኘዉ የኢትዮጵያ ጥናት የትምርት ክፍል በአፍሪቃ ቋንቋዎች እና ባህሎች ላይ ትምህርት የሚሰጥ ሲሆን በኢትዮጵያ ቋንቋዎች የአማርኛ የግዕዝ አልፎ አልፎ የትግርኛ እና የኦሮምኛ ቋንቋ ትምህርት ይሰጣል። በኢትዮጵያ የብራና ጽሑፎች ላይ ጥናትና ምርምር ይካሄዳል። በጀርመን ሀንቡርግ ከተማ በሚገኘዉ የአፍሪቃ በተለይም በኢትዮጵያ ጥናት የትምህርት ክፍል ዉስጥ በምርምር ሥራና የPHD ትምህርታቸዉን በመከታተል ላይ ያሉት አቶ አብርሃም አዱኛ በዕለቱ ዝግጅታችን ጋብዘናል።

Bild: Älteste äthiopische Bibelhandschrift - ist eine Silbenschrift; sie wird im Gegensatz zu den anderen semitischen Schriften von links nach rechts geschrieben. Titel: Die Forschungsstelle Äthiopistik der Universität Hamburg ist für die Aufgabe der Wahrung bedrohter äthiopischer Handschriften wie prädestiniert, weil sie seit langem Quellensicherung in Äthiopien betreibt und sich einen Namen gemacht hat in der Erforschung der Kulturgeschichte des Landes. 1968 wurde in Hamburg deutschlandweit der erste Lehrstuhl für Äthipistik eingerichtet.
ምስል DW/ A.T.Hahn

የኢትዮጵያ ጥናት በጀርመን ብሎም በአዉሮጳ የጀመረዉ በ17ኛዉ ክፍለ ዘመን በጀርመናዊዉ ተመራማሪ ሂዩብ ሩዶልፍ ነዉ። ጀርመናዊዉ ተመራማሪ ሂዩብ ሩዶልፍ ከአባ ጎርጎሪዮስ የአማርኛና የግዕዝ ቋንቋዋን በመማራቸዉም በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ብዙ ሰርተዋል፤ ከ 17 ኛዉ ክፍለ ዘመን የጀመረዉ የኢትዮጵያ ጥናት በተለይ በሀንቡርጉ ዩንቨርስቲ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነዉ። በኢትዮጵያ ጥንታዊ የብራና ጽሁፎች ላይ ከተለያዩ የአዉሮጳ ምሁራን ጋር በሀንቡርግ ዩንቨርስቲ ጥናት የሚያደርጉት አቶ አብርሃም አዱኛ፤ ስለ ጥንታዊዉ የኢትዮጵያ የብራና ጽሑፍ ከኢትዮጵያዉያን ይልቅ ምዕራባዉያኑ ያዉቁታል ከፍተኛ ምርምርም አድርገዉበታል፤

Bild: Älteste äthiopische Bibelhandschrift - ist eine Silbenschrift; sie wird im Gegensatz zu den anderen semitischen Schriften von links nach rechts geschrieben. Titel: Die Forschungsstelle Äthiopistik der Universität Hamburg ist für die Aufgabe der Wahrung bedrohter äthiopischer Handschriften wie prädestiniert, weil sie seit langem Quellensicherung in Äthiopien betreibt und sich einen Namen gemacht hat in der Erforschung der Kulturgeschichte des Landes. 1968 wurde in Hamburg deutschlandweit der erste Lehrstuhl für Äthipistik eingerichtet.
ምስል DW/ A.T.Hahn

በአዉሮጳ ሕብረት የሳይንስ ተቋማት የሚደገፈዉ የኢትዮጵያ ጥንታዊ የብራና ፅሁፎች መዘርዝር የመሥራት ማለትም ካታሎግ የማድረግ ፕሮዤ ላይ በጀርመን ሐንቡርግ ዮንቨርስቲ ዉስጥ የሚሳተፉት የዕለቱን እንግዳ አቶ አብርሃም አዱኛን እናመሰግናለን። ሙሉ ቅንብሩን የድምፅ ማድመጫዉን በመንካት ይከታተሉ!

አዜብ ታደሰ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ