1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ፊደል ካስትሮ አረፉ

ቅዳሜ፣ ኅዳር 17 2009

የቀድሞው የኩባ ፕሬዝዳንት እና አብዮታዊው ፊደል ካስትሮ በ90 ዓመታቸው ኩባ መዲና ሐቫና ውስጥ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

https://p.dw.com/p/2TJ5Y
Kuba Fidel Castro
ምስል picture-alliance/dpa/A. Ernesto

የቀድሞው የኩባ ፕሬዝዳንት እና አብዮታዊው ፊደል ካስትሮ በ90 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ኩባን በፕሬዝዳንትነት የሚመሩት ታናሽ ወንድማቸው ራውል ካስትሮ ዜና ረፍታቸውን በአገራቸው ብሔራዊ የቴሌቭዥን ጣቢያ ዛሬ ይፋ አድርገዋል። ኩባም እስከ ኅዳር 25 ቀን 2009 ዓ.ም. የሚዘልቅ ብሔራዊ ሐዘን አውጃለች።

ፊደል ካስትሮ በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት ወታደሮቻቸውን ወደ ኢትዮጵያ እና አንጎላ በማዝመት ከአብዮታዊ ጓዶቻቸው ጎን ተሰልፈው አዋግተዋል። የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ለገነቡት ከፍተኛ የጦር ሰራዊት ድጋፍ አድርገዋል።

ለ47 አመታት ኩባን የመሩት እና አስር የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንቶች ሲፈራረቁ የታዘቡት ካስትሮ በጤና መታወክ ምክንያት መንበረ ስልጣናቸውን ለታናሽ ወንድማቸው ራውል ካስትሮ ያስረከቡት ከአስር አመት በፊት ነበር። 
 

እሸቴ በቀለ

ማንተጋፍቶት ስለሺ