1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ፍርድ ቤት የቀረቡት የኬንያው ምክትል ፕሬዚዳንት

ማክሰኞ፣ ጳጉሜን 5 2005

የኬንያው ፕሬዚዳንት ዑሑሩ ኬንያታ ምክትል ፣ ዊልያም ሩቶና አብሮአቸው የተከሰሰው ጋዜጠኛ ጆሽዋ ሳንግ፤ ፣ በዛሬው ዕለት ደን ኻኽ ውስጥ ከዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች መርማሪ ፍርድ ቤት ፊት ቀርበው በሰጡት ቃል፤ በሰብአዊነት ላይ የፈጸምነው ወንጀል

https://p.dw.com/p/19fdm
Kenya's Deputy President William Ruto speaks with broadcaster Joshua arap Sang (R) in the courtroom before their trial at the International Criminal Court (ICC) in The Hague September 10, 2013. Ruto appeared at the International Criminal Court on Tuesday for the opening of his trial on charges of co-orchestrating a post-election bloodbath five years ago. Ruto and his co-accused, the broadcaster Joshua arap Sang, could face long prison terms if convicted. To the left is defense counsel Karim Khan. REUTERS/Michael Kooren (NETHERLANDS - Tags: CIVIL UNREST POLITICS CRIME LAW)
ዊልያም ሩቶና ጋዜጠኛ ሳንግምስል Reuters

የለም አሉ። በሥልጣን ላይ ያለ አንድ የመንግሥት አባል ከተጠቀሰው ፍርድ ቤት ሲቀርብ ፣ ሩቶ የመጀመሪያው ናቸው። በኬንያው ምክትል ፕሬዚዳንት ላይ ስለቀረበው ክስና ስለሰውየው ማንነት ተክሌ የኋላ ባጭሩ ያጠናቀረውን ቀጥሎ እናቀርባለን።

የ 46 እና የ 38 ዓመት ጎልማሶች፣ ፖለቲከኛው ዊልያም ሩቶና ጋዜጠኛ ሳንግ ፣

Kenya's Deputy President William Ruto (C) smiles as he sits in the courtroom before his trial at the International Criminal Court (ICC) in The Hague September 10, 2013. Ruto appeared at the International Criminal Court on Tuesday for the opening of his trial on charges of co-orchestrating a post-election bloodbath five years ago. Ruto and his co-accused, broadcaster Joshua arap Sang, could face long prison terms if convicted. To the left is defense counsel Karim Khan. REUTERS/Michael Kooren (NETHERLANDS - Tags: ELECTIONS POLITICS CRIME LAW)
ምስል Reuters

የቀረበባቸው ክስ፤ በታኅሳስ ወር 2000 ዓ ም ፣ በኬንያ ምርጫ ከተካሄደ በኋላ፣ የያኔዎቹ ተፎካካሪዎች ፤ ምዋይ ኪባኪና ራይላ ኦዲንጋ መካከል ፣ እያንዳንዳቸው አሸናፊ መሆናቸውን የገለጡበት ሁኔታ ማከራከሩን እንደቀጠለ ፤ የጎሣዎች ሁከት ሲቀሰቀስ፤ የወንጀል ተግባራትን በማቀነባበር፤ ግድያ እንዲፈጸም ፣ እንዲሁም ሰዎች ከቀየአቸው እንዲፈናቀሉና እንዲሳደዱ አድርገዋል የሚል ነው።

ያኔ በተወሰደው የኃይል እርምጃ ፤ ቢያንስ 1,200 ሰዎች ሕይታቸውን ሲያጡ፤ 600,000 ቤት- ንብረታቸውን ትተው ፤ ቀየአቸውን ለቀው መሰደድ ግድ ሆኖባቸዋል።

በኪኩዩ ብሔርና በሉዎ ብሔር በተለያዩትም ብሔረሰቦች መካከል ጥላቻ እንዲቀሰቀስ ያደረጉት የፓርቲዎች ተወካዮች መሆናቸው ነው የተመለከተው። የአሁኑ ፕሬዚዳንት ዑሁሩ ኬንያታም፣ በ 2000 ዓ ምህረቱ ምርጫ፤ የቀድሞውን ፕሬዚዳንት ምዋይ ኪባኪን በመደገፍ ፣ የብሔራቸው አባላት የሆኑትን ኪኩዩዎችን በማነሣሣት ያኔ ለተፈጸመው ግድያና መፈናቀል ኀላፊ ናቸው ተብለው ነው የተከሰሱት ። የእርሳቸው ጉዳይ በደን ኻኹ ፍርድ ቤት ፍርድ ቤት የሚቀርበው ኅዳር 3 ቀን 2006 ነው።

FILE - In this Monday, Jan. 28, 2008 file photo, Kenyan men from the Luo tribe armed with machetes and rocks enforce a makeshift roadblock, searching passing vehicles for Kikuyus trying to flee the town in order to kill them, during post-election violence on the main road to the Ugandan border near the airport in Kisumu, Kenya. Kenya's deputy president William Ruto left for The Hague on Monday, Sept. 9, 2013 to face trial Tuesday on charges of crimes against humanity that he helped orchestrate the country's 2007-08 postelection violence during which more than 1,000 Kenyans were killed during weeks of vicious tribe-on-tribe attacks following a disputed presidential vote in late 2007 that took Kenya to the brink of civil war. (AP Photo/Ben Curtis, File)
ምስል picture-alliance/AP Photo

የካሌንጂን ብሔረሰብ አባል ዊልያም ሩቶ፣ ተሰጥዖ ያላቸው መሪ መሆናቸው በብዙ ኬንያውያን ዘንድ ይነገርላቸዋል። ኬንያዊው የፖለቲካ ጉዳዮች ተንታኝ ፣ ጆሴፋት ማጉት እንደሚሉት፤ የህይወት ታሪካቸው ፤ ለብዙ ድሆች ኬንያውያን አርአያነት ያለው ነው። ጠንክሮ መማርና መሥራትን በተጨባጭ ሁኔታ ያሳዩ ሰው ናቸውና!

በሰሜናዊው ምዕራብ ኬንያ የተወለዱት ተወልደው ሩቶ፤ በትምህርታቸው ጥሩ ውጤት እያስመዘገቡ ፤ በትርፍ ጊዜያቸውም ምግብ በመሸጥ ፣ ለትምህርታቸው ይከፍሉላቸው የነበሩትን ወላጅ አባታቸውን እየደገፉ ያደጉ ናቸው። እ ጎ አ በ 1990ኛዎቹ ዓመታት መግቢያ ላይ ፤ የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ዳንኤል አረፕ ሞይ፣ በተጠቀሰው የአገሪቱ ክፍል የሩቶን ት/ቤት ሲጎበኙ ፤ በተካሄደ የትምህርት ቤት የጸሎት ሥነ ሥርዓት ወጣቱ ተማሪ መሪ ሆነው መቅረባቸውን ትጉኅ ሆነው መታየታቸው አረፕ ሞይን ሳያስደንቅ አልቀረም። ከዚያ በኋላም ነበረ እ ጎ አ በ 1992 በተካሄደው ነጻ ምርጫ ለፓርቲያቸው ወጣቶችን እንዲያደራጁ ሞይ ኀላፊነት የሰጧቸው። አሁን የምክትል ፕሬዚዳንትነት ሥልጣን እስኪደርሱ የኮተኮቷቸው አረፕ ሞይ ናቸው ማለት ይቻላል። በኬንያ የጀርመኑ ፣ የኮንራድ አደናዎር ድርጅት ተጠሪ ካeቴን ዱምል፣ ሩቶ ፤ የሚፈልጉትን የሚያውቁ ሰው ናቸው ይላሉ።

«አቶ ዊልያም ሩቶ፣ የፖለቲካ ስልት በመቀየስ ተሰጥዖ ያላቸው ሰው ናቸው። በመጠየቅና እርዳታ በማግኘትም አያሌ ጉዳዮችን አከናውነዋል። በራሳቸው ጎሳ መካከል ብቻ ሳይሆን ፣ ባጠቃላይ በኬንያ የፖለቲካው ሂደት እንዲሻሻል አስተዋጽዖ ያደረጉም ናቸው። »

Kenya's Deputy President William Ruto reacts as he sits in the courtroom before their trial at the International Criminal Court (ICC) in The Hague on September 10, 2013. Ruto appeared at the International Criminal Court on Tuesday for the opening of his trial on charges of co-orchestrating a post-election bloodbath five years ago. Ruto and his co-accused, the broadcaster Joshua arap Sang, could face long prison terms if convicted. AFP PHOTO/Michael Kooren (POOL) (Photo credit should read MICHAEL KOOREN/AFP/Getty Images)
ዊልያም ሩቶምስል Michael Kooren/AFP/Getty Images

ዱምል፣ እንደሚሉት ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ፣ ምክትል ፕሬዚዳንት እስከመሆን የደረሱት የ 6 ልጆች አባት ዊልያም ሩቶ፣ ተወዳጅ ናቸው። ጠንክረው በመሥራት ከድህነት ኑሮ ተላቀው እዚህ ደረጃ ለመድረስ በመቻላቸው የሚያደንቁ ጥቂቶች አይደሉም። ተግባራቸው ሁሉ አዎንታዊ ገጽ ብቻ የነበረው ባይሆንም ፣ ኬንያውያኑ ይበልጥ የሚያተኩሩት፤ በጥረታቸውና በደረሱበት ደረጃ ላይ ሆኗል። በሌላ በኩል ደግሞ በክርስትና እምነታቸው ፤ በጰንጠቆስጤ ቤተ ክርስቲያን በትጋት መሳተፋቸው በእምነታቸው ተጋሪዎች ዘንድ ተወዳጅነትን አትርፎላቸዋል። አሁንም ካርስተን ዱዑመል

«የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ መሆናቸው በአደባባይ እንዲታይላቸው የሚያደርጉ ናቸው፤ሩቶ! በተለይ እ ጎ አ የ 2012 ምርጫ ከተቃረበበት ጊዜ አንስቶ ፣ በየጊዜው ክርስቲያን መሆናቸውን በይፋ ነበረ የሚያሳውቁት።»

የኬንያ ምክትል ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ደን ኻኽ የቀረቡት ፤ በአፍሪቃው ክፍለ ዓለም የጦር ወንጀለኞች መርማሪው ፍርድ ቤት አድሎአዊ ነው የሚለው አመለካከት በተስፋፋበት ወቅት ነው። ለምሳሌ ያህል እ ጎ አ በ 2002 የተከሰሱ 18 ግለሰቦች ሁሉም ከአፍሪቃ ክፍለ ዓለም ብቻ መሆናቸው ተመዝግቦአል። የጦር ወንጀለኞች መርማሪው ፍርድ ቤት ጠ/ዐቃቤ ህግ ፤ ጋምቢያዊቷ ፋቱ ቤንሱዳ ግን ፣ ይህ በአፍሪቃ ክፍለ ዓለም ላይ ወይም በኬንያውያን ጉዳይ ጣልቃ መግባት አይደለም ፤ ዓላማው ፣ የኅይል እርምጃ ሰለባዎች ለሆኑት ቤሰቦች ፍትኅ ለማስገኘት ነው ብለዋል።

ተክሌ የኋላ

አዜብ ታደሰ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ