1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ፕሬዚዳንት ዮአሂም ጋዉክ በይፋ ስልጣን ለቀቁ

ሰኞ፣ መጋቢት 11 2009

የጀርመኑ ፕሬዚዳንት ዮአሂም ጋዉክ ከአምስት ዓመት ሥልጣን በኋላ ዛሬ በወታደራዊ ስነ ስርዓት በበርሊኑ የ«ቤሊቪዉ» ቤተ መንግሥት በይፋ ተሸኙ። ወታደራዊ ስነ ስርዓቱ የጀርመን ጦር ከሚያዘጋጃቸው ስነ ስርዓቶች ከፍተኛው ነው።

https://p.dw.com/p/2ZS5u
Belgien Bundespräsident Joachim Gauck und seine Lebensgefährtin Daniela Schadt zum Staatsbesuch beim belgischen Königspaar
ምስል picture-alliance/dpa/P. van Katwijk

በዝግጅቱ ላይ በሃገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች በነፃ በጎ አገልግሎት የሚሰጡ 300 ሰዎችን ጨምሮ ባጠቃላይ 600 እንግዶች እንደተገኙ ታዉቋል። ጋዉክ ከዚህ ቀደም በተደረገላቸዉ ቃለ ምልልስ ከእያንዳንዱ ማኅበረሰብ ጎን እንደሚቆሙ ተናግረዋል። 
« ሥልጣኔን ብለቅም የእያንዳንዱ ኅብረተሰብ አካል ሆኜ ከፖለቲከኞች ጎን ይህ የኛ ዴሞክራሴ ነዉ ይህ የኛ ነፃነት ነዉ ብዬ እናገራሉ።»  
የ 77 ዓመቱ ፕሬዚዳንት ዮአሂም ጋዉክ በእድሜያቸው ምክንያት ለሁለተኛ የስልጣን ዘመን እንደማይወዳደሩ አሳውቀው ነዉ ስልጣኑን የሚለቁት።  ጋውክን የሚተኩት የቀድሞዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር ባለፈዉ እሁድ በይፋ ስልጣኑን ተረክበዋል።     

አዜብ ታደሰ

ኂሩት መለሰ