1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

1 ሺህ 440ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በድምቀት ተከበረ 

ማክሰኞ፣ ግንቦት 27 2011

1 ሺህ 440ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በመላዉ ኢትዮጵያ በድምቀት ተከበረ። በተለይም መዲና አዲስ አበባ ስቴዲዮም ዉስጥና ዙርያዉን ከማለዳው ጀምሮ በታላቅ ሃይማኖታዊ ስርዓት የእምነቱ ተከታዮች፣ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተከብሮአል።

https://p.dw.com/p/3JoKJ
Äthiopien Addis Abeba Muslime Feiern Eid Al-Fitr
ምስል DW/G. Tedla


በበዓሉ በአዲስ አበባ ከተማም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ቀዳሚ ሙፈቲ ሃጂ ኡመር እንድሪስ እና የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ተገኝተዉ ንግግር አድርገዋል።
በበዓሉ ተቀዳሚ ሙፈቲ ሃጂ ኡመር እንድሪስ ባስተላለፉት መልዕክት የዘንድሮዉ የኢድ አልፈጥር በዓል ሰላምና አንድነት የታየበት መሆኑን ገልፀዋል።ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐብይ አሕመድን ጨምሮ ክርስቲያን ወንድሞችና እህቶች የኢድ ሶላት መስገጃ ቦታን ለህዝበ ሙስሊሙ በማፅዳት ላሳዩት ቀና ትብብር አመስግነዋል። 1 ሺህ 440ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል ህዝበ ሙስሊሙ በአዲስ አበባ ከተማ በሚከናወኑ የፅዳት፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትና የችግኝ ተከላ ስራዎች እንዲሳተፍ ም/ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ ጥሪ አስተላልፈዋል።
በዓሉን ምክንያት በማድረግ የሸገር እና አንበሳ የከተማ አውቶቡሶች ከተለያዩ የከተማዋ አቅጣጫዎች የኢድ ሶላት ወደ ሚደረግበት የአዲስ አበባ ስቴዲየም የደርሶ መልስ የነፃ አገልግሎት እንደሚሰጡ የአዲስ አበባ ከንቲባ ፅ/ቤት በትናንትናዉ ዕለት በፌስ ቡክ ገፁ ገልፆ ነበር።

Äthiopien Addis Abeba Muslime Feiern Eid Al-Fitr
ምስል DW/G. Tedla
Äthiopien Addis Abeba Muslime Feiern Eid Al-Fitr
ምስል DW/G. Tedla
Äthiopien Addis Abeba Muslime Feiern Eid Al-Fitr
ምስል DW/G. Tedla

ጌታቸዉ ተድላ 
አዜብ ታደሰ