1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

125ኛዉ የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በባሕርዳር

ማክሰኞ፣ የካቲት 23 2013

ከተናጋሪዎቹ አንዱ የአማራ  ክልል አባት አርበኞች ማሕበር ሊቀመንበር አቶ ዳኝነት አያሌዉ «የተማረዉ ክፍል ከዘር ፖለቲካና ሐገር ከመበጥበጥ» እንዲታቀብ አደራ ብለዋል

https://p.dw.com/p/3q6bw
Äthiopien Adwa  125. Unabhängigkeitstag
ምስል Alemnew Mekonnen/DW

«የተማረዉ ክፍል ሐገር ከመብጥበጥ መታቀብ አለበት» አባት አርበኛ

                                 

125ኛዉ የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በአማራ መስተዳድር ባሕርዳር ዉስጥም በዓሉ በደማቅ ሥርዓት ተከብሯል።የባሕርዳሩ ወኪላችን ዓለምነዉ መኮንን እንደዘገበዉ እንደ አዲስ አበባዉ ሁሉ በባሕሩ በዓለም ላይ ወጣቶች፣ አባት አርበኞችና የአማራ ክልል ባለስልጣናት ተገኝተዋል።የአባት አርበኞችና የክልሉ ባለስልጣናት  በየተራ ንግግር አድርገዋልም።ከተናጋሪዎቹ አንዱ የአማራ  ክልል አባት አርበኞች ማሕበር ሊቀመንበር አቶ ዳኝነት አያሌዉ «የተማረዉ ክፍል ከዘር ፖለቲካና ሐገር ከመበጥበጥ» እንዲታቀብ አደራ ብለዋል።

ዓለምነዉ መኮንን

ነጋሽ መሐመድ

ማንተጋፍቶት ስለሺ