1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

19ኛዉ የኢትዮጵያ ጥናት ጉባዔ በዋርሶ

ሐሙስ፣ መስከረም 13 2008
https://p.dw.com/p/1Gd7y

ፖላንድ ዋርሶ ላይ ስለተካሄደዉ ስለ 19ኛዉ የኢትዮጵያ ጥናት ዓለም አቀፍ ጉባዔ የነገሩን የኢትዮጵያ የጥናትና ምርምር ተቋም ዳይሬክተር ዶክተር አህመድ ሀሰን ነበሩ ጤናይስጥልኝ አድማጮች እደምን አመሻችሁ። የጥንታዊ ቅርሶችና ታሪክ ባለቤት የሆነችዉ ኢትዮጵያ ከረጅም ጊዜ አንስቶ የታሪክ የቅርስ ተመራማሪዎችን ትኩረት እንደሳበች ናት። ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚካሄዱት የተለያዩ ጥናቶች ግብዓትነት ትልቅ አስተዋፅኦን ማድረጉም ይታወቃል። ለዚህም ከ60 ዓመት በላይ የሆነዉ የኢትዮጵያ ጥናት ዓለም አቀፍ ጉባዔ ተጠቃሽ ነዉ። ስለጉባኤዉ ፋይዳ ኢትዮጵያዉያንና ጀርመናዊ ተሳታፊን አነጋግረንናል።