1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

3ተኛው ዙር የግሪክ ብድር

ዓርብ፣ ነሐሴ 8 2007

መርሃ-ግብሩ ከፀደቀ ግሪክ በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት ውስጥ የ 85 ቢሊዮን ዩሮ ብድር ታገኛለች ። በምትኩ ግሪክ የወጪ ቅነሳና የቀረጥ ጭማሪ ማድረግ ይጠበቅባታል ። እነዚህን የቁጠባ እርምጃዎች በመቃወም ከ40 በላይ የግሪክ ገዥ ፓርቲ ሲሪዛ አባላት መርሃግብሩን ሳይደግፉ ቀርተዋል ።

https://p.dw.com/p/1GFgK
Griechenland Beratung Hilfspaket Parlament
ምስል Reuters/C. Hartmann

[No title]

የግሪክ ፓርላማ አባላት ለግሪክ የታቀደውን ሶስተኛ ዙር የብድርና እርዳታ መርሃ ግብር ተቀብለው ዛሬ አጽድቀዋል ። የግሪክ የህዝብ እንደራሴዎች መርሃ ግብሩን በ222 የድጋፍ ድምፅ የተቀበሉት ትንናት ለሊት ከተካሄደ የጋለ ክርክር በኋላ ነው ። የዩሮ ተጠቃሚ ሃገራት የገንዘብ ሚኒስትሮች ደግሞ ዛሬ በመርሃ ግብር ላይ ተወያይተው ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል ። መርሃግብሩ ከፀደቀ ግሪክ በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት ውስጥ 85 ቢሊዮን ዩሮ ብድር ታገኛለች ። በምትኩ ግሪክ የወጪ ቅነሳና የቀረጥ ጭማሪ ማድረግ ይጠበቅባታል ። እነዚህን የቁጠባ እርምጃዎች በመቃወም ከ40 በላይ የግሪክ ገዥ ፓርቲ ሲሪዛ አባላት መርሃግብሩን ሳይደግፉ ቀርተዋል ። ስለ አወዛጋቢው 3ተኛው ዙር የግሪክ ብድር ና በሲሪዛ ፓርቲ አባላት መካከል ስለ ተፈጠረው ልዩነት የብራሰልሱን ወኪላችንን ገበያው ንጉሴን በስልክ አነጋግሬዋለሁ ።

ገበያው ንጉሴ

ኂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ