400 የሒሳብ መመዝገብያ ማሽኖች ተሰወሩ
ሐሙስ፣ ኅዳር 6 2011ማስታወቂያ
ከኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር 400 የሒሳብ መመዝገብያ ማሽኖች ከእይታ መሰወራቸዉ ተመለከተ። የማሽኖቹ ሥራ በመሰወሩ መንግስት ወደ 4 ቢሊዮን ብር ገቢን እንዳሳጣዉ ተመልክቶአል። ይህ የሆነዉ ሽያጭ ሳይከናወን ደረሰኝ በመሸጥ ብቻ የደረሰ ብክነት መሆኑ ነዉ የተነገረዉ። የገቢዎች ሚኒስቴር 4 ቢሊዮን ብር ማጣቱን ቢያምንም የሒሳብ ባለሞያዎች የጥፋቱ መጠን ሳይጨምር እንደማይቀር ነዉ የሚናገሩት። ዝርዝር ዘገባዉን የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ልኮልናል።
ዮሃንስ ገብረግዚአብሔር
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሐመድ