1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስደት በስደተኞች በጥበብ ሲገለጽ

ዓርብ፣ ታኅሣሥ 19 2011

ስለስደት እና ስደተኞች በተለያዩ የፈረንሳይ መገናኛ ብዙሃን፣ በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና በሰብዓዊ ድጋፍ ሰቺ ተቋማት ከሚነገረው ቀውስ በተለየ ስለጉዳዩ የሚያመለክት ትዕይንት ፈረንሳይ ዉስጥ ለእይታ ቀረበ።

https://p.dw.com/p/3Ajrh
Türkei Notunterkunft von Flüchtllingen
ምስል DW/D. Heinrich

ስደተኞች የተካተቱትበት የጥበብ ትርዒት በፈረንሳይ

ስደተኞች ስለስደት ጉዟቸው ጥበባዊ በሆነ መልኩ የሚገልፁበት የጥበብ ትዕይንት በፈረንሳይዋ የዲጆ ከተማ በሚገኘው የዲጆ ረቂቅ ጥበብ ቤተመዘክር ውስጥ ለጎብኝዎች ሰሞኑን ይፋ የሆነው። የተገን ጠያቂዎች ማረፊያ ማዕከል ወይማ ካዳ ተብሎ በምህጻሩ በሚታወቀው ተቋም ውስጥ ይገኙ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የሌሎች ሃገራት ተሰዳጆችም በዲጆ ከሚገኙ የፈረንሳይ የጥበብ ባለሙያዎች ጋር በመሆን ነው በአንድ ላይ ሥራቸውን ለተመልካች ያቀረቡት። ትርዒቱ ስደተኞቹ በመረጧቸው የጥበብ የሥዕል ሥራዎች ላይ በስነጽሑፍ እና በሙዚቃ ተቀነባብሮ የቀረበ ሲሆን በተመልካቹም ዘንድ ስሜትን በመንካት ከፍተኛ ተቀባይነት ማግኘቱም ተነግሯል። ሃይማኖት ጥሩነህ ከፓሪስ ዝርዝር ዘገባ ልካልናለች።

ሃይማኖት ጥሩነህ

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ