1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በመጪው ዓመት ምርጫ ማካሄድ ይቻል ይሆን?

እሑድ፣ ግንቦት 25 2011

ኢትዮጵያ በሕገመንግሥቱ መሠረት በመጪው ዓመት ግንቦት ወር ምርጫ ታካሂዳለች ተብሎ ይጠበቃል። የቦርድ አባላቱን ለማሟላት ገና በሂደት ላይ የሚገኘው ብሔራዊ የምርጫ ለምርጫ ሥራ ማስኬጂያ ከ3,5 ቢሊየን ብር በላይ ገንዘብ በጀት ጠይቋል። መንግሥት እና አንዳንድ ፓርቲዎች ምርጫው በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሠረት መካሄድ ይኖርበታል ባይ ናቸው።

https://p.dw.com/p/3JZzM
Äthiopien Wahlen 2015
ምስል DW/E. Bekele

«ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የመጨረሻው መገለጫ ነው»

በሌላ ወገን ደግሞ ምርጫ ለማካሄድ አስቀድሞ መሟላት የሚገባቸው መሠረታዊ ጉዳዮች መኖራቸውን በመዘርዘር ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለማካሄድ ተፈላጊውን ማከናወን ይቀድማል የሚሉ ወገኖች አሉ። የሕዝብ እና ቤት ቆጠራ፣ የምርጫ አስፈጻሚ መዋቅሮች ዝግጅት፣ በየክልሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያልተገደበ እንቅስቃሴ ማድረግ ፤ የሕግ እና የፍትህ ተቋማት ገለልተኛነት፣ በሀገሪቱ የሚታየው ያልሰከነ የመፈናቀል እና የፀጥታ ጉዳይን  ቅድሚያ ሰጥቶ ደርዝ ማስያዝያ እንደሚገባ በማሳሰብም ፤ በዚህ ይዞታ ምርጫ አሁን ዋነኛው አሳሳቢ ጉዳይ እንዳልሆነም ያስረዳሉ። ከ100 የሚበልጡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ባሉባት ሀገር በቦርዱ በኩል እስካሁን አስፈላጊውን አሟልተው የተመዘገቡት 68 ፓርቲዎች መሆናቸውን ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ አስታውቋል። ዶይቼ ቬለ ለዚህ ሳምንት ኢትዮጵያ በመጪው ዓመት ምርጫ ማካሄድ አለባትን? ሲል ውይይት አካሂዷል።  ሙሉውን ውይይት ከድምፅ ዘገባው ያድምጡ።

ሸዋዬ ለገሠ

ልደት አበበ