1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ሳይንስ

ቴክኖሎጂ የምርጫ ስጋት ሲሆን

ረቡዕ፣ ጥቅምት 28 2011

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢንዱስትሪ በበለጹጉት ሀገራት ምርጫ በመጣ ቁጥር የሚነሳ ስጋት አለ። በእነዚህ ሀገራት የምርጫ ሂደቶች በኮምፒውተሮች በሚመራ ስርዓት እንዲቀላጠፍ መደረጉ ምርጫው ላይ ተጽዕኖ ለማሳደር ለሚፈልጉ ሰዎች ዕድል መክፈቱ ነው የስጋቱ መንስኤ። የአሜሪካ የህዝብ እንደራሴዎች ምርጫም ተመሳሳይ ስጋቶች ተንጸባርቀውበታል።

https://p.dw.com/p/37qPL
USA - 2018 Wahl in Missouri
ምስል picture-alliance/AP Photo/St. Louis Post-Dispatch/J. B. Forbes

ቴክኖሎጂ የምርጫ ስጋት ሲሆን

በአሜሪካ ከፕሬዝዳንት ምርጫ በሁዋላ ተከታትሎ በሁለተኛው ዓመት የሚካሄደው የህዝብ እንደራሴዎች ምርጫ አንድ ዓላማ አለው። እርሱም በፕሬዝዳንቱ ስራ ላይ የድጋፍ ወይም ደግሞ ይህን ሰው መቆጣጠር አለብን የሚል የተቃውሞ ማስጠንቀቂያ ያዘለ ነው። ፖለቲከኞች በስልጣናቸው እንዳይባልጉ የመቆጣጠርም ልጓምም ነው። ዘንድሮ ከዚሁ ጋር ሌላው ችግር ህዝቡ የሰጠው ድምጽ በትክክል ተቆጥሯል ወይስ ባልሆነ ምክንያት ተጨብርብሯል የሚል ነው። 

የዕለቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መሰናዷችን የ21ኛውን ክፍለ ዘመን የዲሞክራሲ ስርዓት ጋሬጣ ነው ስለሚባለው ቴክኖሎጂን ተጠቅሞ የምርጫ ውጤቶችን መዛባት ጉዳይ ይዳስሳል። ሙሉ መሰናዶውን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ።  

ይልማ ኃይለሚካኤል

ተስፋለም ወልደየስ